በመንግስትና በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት መካከል የሰላም አማራጭ ለመፈለግ በታንዛንያ ዳሬ ሰላም እየተካሄደ ያለው ንግግር መግባባት እየታየበት እንደሆነ ተመለከተ። በዚሁ ምክንያት የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴንና የፍትሕ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ድርድሩን ትላንት መቀላቀላቸው ተሰምቷል።
ኢትዮ12 የሰላም አማራጭ ንግግሩ ሲጀመር የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት መሪ ሄሊኮፕተር ተዘጋጅቶላቸው ከደንቢዶሎ ወደ ኬንያ ማምራታቸው ንግግሩ ቀደም ሲል ብዙ ርቀት የተኬደበትና ተስፋ የሚሰጥ ስለመሆኑ ማሳያ እንደሆነ ምንጭ ጠቅሳ መዘገቧ ይታወሳል።
” ኦሮሞ ዛሬ ላይ ጠብ መንጃ የሚያስፈጽመው አንዳችም ጉዳይ የለም” የሚሉ መበራከታቸው፣ ወለጋን የመሰለ ለምና ሃብታም ገበሬ ለማኝ መሆኑ፣ የቡና አምራችና ነጋዴ ሃብታም አርሶ አደሮችና ነጋዴዎች መሰደዳቸው፣ ሃብታቸውና ንብረታቸው ተዘርፎ ተመጽዋች መሆናቸው፣ በጥቅል ኦሮሚያ በግፍ የሚገደሉና የሚፈናቀሉ፣ ቤት ንብረታቸው የሚነድና የሚዘረፍባቸው … አንድ ላይ ተዳምሮ ህዝብ በትጥቅ ትግሉ እንደተሰላቸ የሚያሳዩ ምልክቶች በስፋት ታይተዋል።
ከምንም በላይ ግን የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት የሚባለውን ታጣቂ ቡድን የሚመሩት ጃል መሮ በቅርቡ በውጭ አገር ያሉትንና በትግሉ ስም ገንዘብ እይሰበሰቡ እንደሚሰርቁ፣ ለታለመለት ዓላማ እንደማያውሉ አንስተው ክፉኛ መተቸታቸው ድርጅቱ የኢኮኖሚ አቅሙ መዳከሙን የሚያሳይ እንደሆነ አመላካች እንደሆነ ጉድዩን የሚከታተሉ ይናገራሉ።
ሰሞኑንን መንግስት በተደጋጋሚ እንደሚናገረው በኦሮሚያ ክልል ነፍጥ አንስቶ እየተንቀሳቀሰ ያለውን ይህን ሃይል ለማጥፋት ሙሉ ዘመቻ ተከፍቷል። በዚሁ ዘመቻ ቡድኑ ቁሳዊ፣ ሰብዓዊ ኪሳራ እንደደረሰበት፣ በቁጥጥሩ ስር አድርጓቸው የነበሩ አካባቢዎች ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ መነጠቁን፣ አመራሮቹን ጨምሮ በርካታ መማረካቸውና እጅ መስጠታቸው መንግስት በተለይም የአገር መከላከያ እያስታወቀ ነው። የሎጅስቲክ ምንጩም መዳከሙን መንግስት ለመጀመሪያ ጊዜ ሰሞኑን አመልክቷል።
ከትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ጋር በጣምራ አብሮ ሲሰራ የነበረውና ከፍተኛውን በጀትም ከትህነግ ያገኝ እንደነበር የሚነገርለት የጃልመሮ ቡድን ትህነግ ለሰላም እጁን ከሰጠ በሁዋላ በጀት እያጠረው እንደሆነ በወቅቱ መገለጹ አይዘነጋም። ይህንኑ ተከትሎ ነበር ከስድስት ወር በፊት የመጀመሪያ የሰላም ንግግር የተደረገው። ምንም እንኳ ንግግሩ በሙሉ ስምምነት ባይቋጭም ክማሮው ለቀጣይ ውይይት በር ከፋች እንደሆነ ከሁለቱም ወገኖች መነገሩ ይታወሳል።
የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ተደራዳሪ ቡድን በዋና አዛዡ ድሪባ ኩና ወይም ጃል መሮና ምክትላቸው ጃል ገመቹ አቦዬ በንግግሩ እየተሳተፉ እንደሆነ ቡድኑ ባወጣው መግለጫ ይፋ አድርጎል። ዝርዝር መግለጫ እንደሚሰጥም አመልክቷል። ንግግሩ በጦር መኮንኖች መካከል በስምምነት በመጠናቀቁ በሚታወቅ ተቋም ይፋ ባይሆንም ከመንግሥት በኩል፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴንና የፍትሕ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ፣ በትናንትና ዕለት መቀላቀላቸው ተሰምቷል።
ቡድኑ ስለድርድሩ ባሰራጨው አጭር መረጃ ንግግሩ በበጎ ገጽታው እየቀጠለ መሆኑን አስታውቋል። ለጉዳይ ቅርብ የሆኑ እንደገለጹት ንግግሩ በስምምነት እንደሚቋጭና ሰላም ለናፈቃቸው ወገኖች መልካም ዜና እንደሚሆን እምነታቸውን ገልጸዋል።
ጃልመሮ “ለምን ይደራደራል” የሚሉና ” እንዴት ከአሸባሪ ጋር መንግስት ለንግግር ህይቀመጣል” በሚል ከወዲሁ የራሳቸው አጅንዳ ባላቸው በኩል የሚሰራጨው ቅስቀሳ ውጤቱን በጉጉት ከሚጠብቁት እኩል ገና ለገና አጀንዳው በሰላም ከተቋጨ አሳባቸው ሊጨነግፍ እንደሚችል የሰጉ ብዙ ናቸው።
በንቅናቄ ስም በሚጠራ የማህበራዊ ሚዲያ ላይ ” የኦሮሚያን ጉዳይ ጨርሰው በሙሉ ሃይላቸው አማራና ኤርትራ ላይ ሊዘምቱ ነው” የሚል አስተየተ የሚያሰራጩም ታይተዋል።
በተመሳሳይ ” በነካ እጃችሁ አምራ ክልል ላይም ብዙ ኪሳራ ሳይደርስ የሰላም ንግግር እንዲደረግ ግፊት ይደረግ” የሚሉ ሰላም ወዳዶች እጅግ በርካታ ናቸው።
- አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱበዙፋን ኡርጋ ደራሲነት የተጻፈውን ሌንጮ ለታ ትግል ሕይወቱ መጽሐፍን አነበብኩት። መጽሐፉ በ471 ገጾች እና በሦስት ክፍሎች ተቀንብቧል። የመጀመሪያው ክፍል ከልጅነት እስከ ትግል ዋዜማ… Read more: አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱ
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም። ይህ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው







