በኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ አጣቢዎችን ማንነት ለማወቅ ከባህር ማዶ ቢሮ ከፍተው ዶላር የሚሰበስቡትን ከመጠርሪያ ስማቸው በመነሳት መለያየት ቀላል ነው። በውጭ አገር ሆነው ፖለቲካ በመቀመርና ለፖለቲካ ቅመራው እርዳታ በመጠየቅ የዲጂታል ለማኝ የሆኑት ቢያንስ ይህን ስራ ቢሰሩ እንደሚሻላሸው ምክር የሚሰጡት ስራው እጅግ ከፍተኛ ገንዘው ወደ ሌላ አገር እያሻገረ በመሆኑ ነው።
በዚሁ የምንዛሬ አጠባ ሁለት አበይት ጉዳዮች ይነሳሉ። አንዱ ኢትዮጵያ ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ ኮንትሮባንድ ላይ የተሳተፉ ህዝብ የሚያውቃቸው “የውጭ ዜጎች” በህገወጥ ንግድ በሚሊዮኖች ብር ይሰበስባሉ። የአገሪቱን ኢኮኖሚ ያደቃሉ። ከውጭ ሆነው ምንዛሬ በመቀበል ኢትዮጵያ ውስጥ በኮንትሮባንድ በሚሰብሰበው ብር ከፍተኛ ምንዛሬ ይሰጣሉ።
በዚህ ስራ የተሰማሩት ክፍሎች ከውጭ ገንዘብ ለተላከላቸው ሰዎች ያለው ውድድር፣ ያለቀረጥ ክፍያ በኮንትሮባንድ ያፈሱትን ገንዘብ ወደ ውጭ ገንዘብ በመቀየር ለራሳቸው አገር የውጭ ምንዛሬ ምንጭ እንደሆኑ ስራውን የሚያውቁ በተደጋጋሚ ያስረዳሉ። አዲስ አበባ ከትመው ኢትዮጵያን በሁለት ካራ የሚገዘግዙት እነዚህ ክፍሎች በህገወጥ የውጭ ምንዛሬ ግብይት ላይ በስፋት ከሚሰሩት መካከልም ናቸው። ይህን የኋላ ጉዳይ ያስታወሰው ዛሬ የተሰማው የህገወጥ ዶላር ህትመትና አዘዋዋሪዎች መያዝ ነው።
በአዲስ አበባ በህገወጥ የታተመ የውጭ ምንዛሬ በድብቅ ሲያዘዋውር ነበር የተባሉ ተጠርጣሪ ተይዟል። የመንግስት መገናኛዎች ባሰራጩት በዚህ የሌብነት ዜና የተያዘው ተጠርጣሪ ማንነትና ስም አለመጠቀሱ ጥርጣሬ አስነስቷል። ዜናውን ተከትሎ ” ባትነግሩንም አውቀናቸዋል። ገንዘብ ዝውውር ስር የሚራወጡት ይታወቃሉ” የሚል አስተያየትም ተሰጥቷል።
ከ28ሺህ በላይ ሀሰተኛ የአሜሪካን ዶላር ይዞ ሲንቀሳቀስ የነበረው ግለሰብ ተይዞ ምርመራ እየተጣራበት እንደሚገኝ የቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ሲያስታውቅ፣ ይፋ የተደረገው ተጠርጣሪው ሲጠቀምበት የነበረ በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2- C 32496 አ/አ በሆነ ተሽከርካሪና ኤግዚቢት የተያዘውን ብር ነው።
ስሙ እንዲገለጽ ያልተፈለገው ተጠርጣሪ 284 ባለ መቶ ኖቶች(28 ሺህ 400) ሀሰተኛ የአሜሪካ ዶላር ይዞ ሲንቀሳቀስ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 መክሊት ህንፃ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው በቁጥጥር ስር የዋለው። በተደረገ ፍተሻ ከሃሰተኛ ዶላሩ በተጨማሪ ስታር ሽጉጥ ከ 8 ጥይቶች ጋር ተገኝቶበታል።

በአዲስ አበባ የዶላር አጠባ ላይ በብዛት የተሰማሩ ወገኖች እነማን እንደሆኑ የሚታወቅ በመሆኑ፣ የስም ስወራው ጉዳዩን ለማድበስበስና ታልሞ ሊሆን ይቻላል የሚል ስጋት ያላቸው ” ማንነቱና ስሙ ይገለጽ። ሌብነት ላይ የተተከለ ዲፕሎማሲ ጥንቅር ብሎ ይቅር” የሚል አስተያየት ሰጥተዋል። የአገር ስም ጠርተው ” ሚስጢር አይደለም” ያሉም አሉ።
ሀሰተኛ ገንዘቦችን በማተምና ወደ ገበያ ውስጥ እንዲገቡ በማድረግ የሚፈፀም ወንጀል በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጫና የሚያሳድር በመሆኑ ይህንን ህገ ወጥ ተግባር የሚፈፅሙ ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር ውለው ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ ህብረተሰቡ ለፀጥታ አካላት የሚሰጠውን መረጃና ጥቆማ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክት አስተላልፏል።

በሌላ ተመሳሳይ ዜና ሐሰተኛ የውጭ ሀገራትና የኢትዮጵያን ብር በማተምና በማሰራጨት የተጠረጠሩ የካሜሩንና የጊኒ ዜግነት ያላቸው ግለሰቦቸ በቁጥጥር ስር ዋሉ። ፖሊስ ስማቸውንና ማንነታቸውን ይፋ አደጓል።
ሐሰተኛ የገንዘብ ሕትመትና ስርጭት እንዲሁም ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውሮች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፉና የወንጀል አፈጻጸም ሂደቶቻቸውም እየተወሳሰበ መምጣቱን ተከትሎ በጥናት ላይ የተመሰረተ ምስጢራዊ ክትትል ሲደረግ መቆየቱንና በጸጥታ አካላት እርምጃ መወሰድ መጀመሩን ለመረጃው ቅርበት ያላቸው ምንጮች ጠቁመዋል፡፡
ይህን ተከትሎም ሐሰተኛ የውጭ ሀገራትና የኢትዮጵያን ብር በማተምና በማሰራጨት የተጠረጠሩ የካሜሩንና የጊኒ ዜግነት ያላቸው ሁለት ግለሰቦች እንዲሁም በተባባሪነት ስትሳተፍ የነበረች አንዲት ኢትዮጵያዊት በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው በምርመራ ላይ ይገኛል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 እና 04 እንዲሁም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 የግለሰቦችን ቤት በመከራየት ሐሰተኛ የገንዘብ ሕትመትና ስርጭቱን ሲያከናውኑ መቆየታቸውን ለረጅም ጊዜ በተደረገው ክትትል በመረጃና በማስረጃ በመረጋገጡ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ምንጮቹ ጠቁመዋል፡፡

አልበርት ናዲፎን በሚል ስም የሚጠራው ካሜሩናዊና መሀመድ ጉኒ የተባለው የጊኒ ዜግነት ያላቸው ግለሰቦች ከስድስት ወራት በፊት ወደ ኢትዮጵያ በመግባት ማህሌት ጥላሁን ከተባለች ኢትዮጵያዊት ጋር ሕገወጥ ድርጊቱን ሲያከናውኑ መቆየታቸው ታውቋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ከግለሰቦች ተከራይተው ሐሰተኛ የገንዘብ ሕትመቱን ሲያከናውኑባቸው የነበሩ ሦስት የመኖሪያ ቤቶች በጥናት ተለይተው ሕጋዊ እርምጃ በተወሰደባቸው ወቅት ለወንጀል ድርጊቶቹ የሚጠቀሙባቸው በርካታ ኤግዚቢቶች ተይዘዋል፡፡
ሐሰተኛ ገንዘቦቹን ለማተም የሚያገለግሉ ልዩ ልዩ ቁሶች፣ ፈሳሽ ኬሚካሎች፣ፓውደሮች፣ሐሰተኛ ገንዘቦች፣ የዶላር ማረጋገጫ ቴስት ላይት፣ ፓስፖርቶች፣ የባንክ ደብተሮች እንዲሁም አደንዛዥ እፅና ሌሎችም ማስረጃዎች ከተያዙት መካከል ይገኙበታል ሲሉ የመንግስት መገናኛዎች ዘግበዋል።
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም። ይህ እስከታተመ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ታዋቂ… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ሰላም… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት በድንገተኛ… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን ዶላር ሃብት “የሂሳብ ባለሙያዎች ስህተት”… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች






