የለንደንን መጠነ-ሥፋት ከ2 እጥፍ በላይ የሚሆን የዓለማችን ትልቁ የበረዶ ግግር ተገምሶ እየሄደ ነው ተባለ፡፡ የበረዶ ግግሩ በፈረንጆቹ 1986 ላይ ከአንታርክቲክ ባሕር ዳርቻ ተቆርሶ በዌድል ባሕር አካባቢ የቆየ ሲሆን፥ ከመጠኑ ግዝፈት አንጻርም ‘የበረዶ ደሴት’ የሚል ስያሜን ይዞ በአካባቢው ከ30 አመታት በላይ ቆይታ አድርጓል። የበረዶ ግግሩ ‘የለንደን’ መጠነ ሥፋት ከሁለት እጥፍ በላይ እንደሚበልጥ ቢቢሲ አስነብቧል፡፡
ከ4 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር በላይ መጠን እና 400 ሜትር መጠነ ውፍረት ያለው የበረዶ ግግር አሁን ላይ በንፋስ እና በመሬት ውስጣዊ ግፊት ከነበረበት ስፍራ ለቆ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ተመራማሪዎች እየገለጹ ነው። አሁን ላይ ግግሩ የአንታርክቲክ ባሕረ ገብ መሬትን ሰሜናዊ ጫፍ እያለፈ መሆኑም ተገልጿል፡፡
ተመራማሪዎች “ኤ23 ኤ” በሚል ሥያሜ የሚያውቁትን የበረዶ ግግር እንቅስቃሴ በቅርበት እየተከታተሉት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ለበርካታ አመታት በባህር ላይ ሰፍር ዳርቻ የነበረው ግግር እንቅስቅሴ ስጋት እያጫረ መሆኑንም ዘገባው አመላክቷል።
ግግሩ አሁን ከያዘው የጉዞ አቅጣጫ አንጻር በደቡብ ጆርጂያ ዳርቻ ላይ ቢያርፍ በሚሊየኖች የሚቆጠሩ የዓሳ እና የባሕር ወፎች ዝርያዎች የመኖሪያ ምኅዳር እና ብዝኃ-ሕይወት ያቃውሳል የሚል ስጋት አሳድሯል፡፡
በሚፈጠረው አዲስ ያልተለመደ ምኅዳርም በብዝኃ ሕይወቱ ውስጥ አዲስ የሚፈለፈሉት የዓሳ እና ዐዕዋፍት ዝርያዎች አኗኗር ፣ አመጋገብ ፣ አስተዳደግ እና እንቅስቃሴ እንደሚቀየር ከወዲሁ መላ ምት አስቀምጠዋል።
ሌሎች አጥኚዎች ደግሞ እየተገፋ የሚመጣው የበረዶ ግግር ሥጋት ብቻ ሳይሆን ዕድልም ነው ይላሉ፡፡
በውስጡ የተለያዩ ማዕድናት የያዘ እንደመሆኑ የብዝኃ-ሕይወቱ የምግብ ሠንሠለት እንዲቀጥል አስተዋፅዖ አለውም ነው የሚሉት፡፡
ፋና
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም። ይህ እስከታተመ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ታዋቂ… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ሰላም… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት በድንገተኛ… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን ዶላር ሃብት “የሂሳብ ባለሙያዎች ስህተት”… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች






