በ1983 ኢህአዴግና ሻእቢያ አዲስ አበባ ሲገቡ የኢትዮጵያን መከላከያ ሰራዊት ከሙሉ መዋቅሩ ጋር “የደረግ” በሚል አፍርሰውት እንደነበር ይታወሳል። ባህር ሃይልና አየር ሃይልን ጨምሮ መከላከያ ዳግም በሪፎርም እንዲደራጁ ከተደረገበት ከዛሬ አምስት ዓመት ጀመሮ በተሰራ ስራ ተቋማቱ ኢትዮጵያን በሚመጥን መልኩ መታነጻቸው እየተገለጸ ነው።
ሰሞኑንን 80ኛ የምስረታ በዓሉን እያከናወነ ያለው አየር ሃይል ” ጥቁር አንበሣ” ከአምስት ዓመት በፊት አዋራ የለበሰ፣ ሞቶ የተገነዘ፣ የተረሳና ምናምንቴ ሆኖ የተጣለ ተቋም ነበር። ለውጡን ተከትሎ አየር ሃይል አዋራው ተጠርጎ፣ ዳወው ተመንጥሮ ነብስ መዘራቱን አንደበት ብቻ ሳይሆን ተግባሩ የሚተርከለት ተቋም ሆኗል።
ዘመናዊ ትጥቅ መታጠቁ ብቻ ሳይሆን በብቃትና በሰው ሃይል፣ በጥራትና በጥልቀት የምርመር ተቋም ሆኖ ኢትዮጵያን በአየር ከሚመጣ ማናቸውም አደጋ ለመታደግ ችሏል። ራሱን በሰው ሃይና አደረጃጀት ያዘመነው አይር ሃይል ዛሬ የቀደመውን ውድቀቱን ለሚመኙ ሁሉ ራስ ምታት የሆነ፣ ለአገር ወዳዶች ደግሞ አለኝታ መሆን የቻለ ተቋም መሆኑ ሃላፊዎቹ ሰሞኑንንበተለያዩ መድረኮች ሲያረጋግጡ ሰንብተዋል።
የ”መከላከያ ዘርፍን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች እየተደረጉ ያሉ ማሻሻያዎች ኢትዮጵያን ለማጽናትና ለማስቀጠል ወሳኝ ናቸው ” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተናገሩትም በዚሁ መነሻ ነው።
የመከላከያ ዘርፍን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች እየተደረጉ ያሉ ማሻሻያዎች ኢትዮጵያን ለማጽናትና ለማስቀጠል ወሳኝ ናቸው ሲሉ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐቢይ አሕመድ ያስታወቁት በዚሁ በሰማንያ ስምንተኛው የምስረታ በዓለ ላይ ነው።
የኢትዮጵያ አየር ኃይል 88ኛ ዓመት የምስረታ በዓል የማጠቃለያ ሥነ-ሥርዓት በቢሾፍቱ አየር ኃይል ጠቅላይ መምሪያ በተካሄደበት ወቅት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐቢይ አሕመድ፣ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላና ምክትላቸው ጀነራል አበባው ፣ የመከላከያ ሚኒስትር ዶክተር አብርሃም በላይ፣ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች አየር ኃይል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ኢብራሒም ናስር፣ ጄኔራል መኮንኖች፣ የአፍሪካ አየር ኃይል አዛዦች የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ዝግጅቱ የተከበረበት አግባብ እጅግ ከፍተኛና አህጉርና ዓለም ዓቀፍ ይዘት የተላበሰ በመሆኑ ሰፊ የሚዲያ ሽፋንም አግኝቷል።
የኢትዮጵያ አየር ኃይል 88ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ታላቅ አገር ታላቅ ተቋም የመገንባትና የማጽናት ምልክት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልፀዋል። ኢትዮጵያ የአየር፣ ምድርና ባህርን ጨምሮ በሁሉም መስኮች ወታደራዊ አቅሟን እየገነባች እንደምትገኝ አመልክተዋል።
በኢትዮጵያ የመከላከያ ዘርፍን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች እየተደረጉ ያሉ ማሻሻያዎች አገሪቷን ለማጽናትና ለማስቀጠል ወሳኝ ሚና እንዳላቸው ተናግረዋል።
ለቀጣዩ ትውልድ ታላቅ አገርና ታላቅ ተቋም ለማስተላለፍ መንግሥት አበክሮ እየሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል።
ወቅቱን የዋጀ ወታደራዊ ኃይል መገንባት በአዳዲስ ስልቶች የሚመጡ ጥቃቶችን ለመመከት ያስችላል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለዚህም ሁሉም ወገን የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢፌዴሪ አየር ኃይል አቅሙ እንዲገነባ አስተዋጽዖ ላደረጉ አካላትም ምስጋና አቅርበዋል።
የአየር ኃይሉ 88ኛ ዓመት የምስረታ በዓል “በመስዋዕትነት ሀገርን የዋጀ፤ የኢትዮጵያ አየር ኃይል” በሚል መሪ ኃሳብ ከኅዳር 20 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ሲከበር ቆይቷል።
- አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱበዙፋን ኡርጋ ደራሲነት የተጻፈውን ሌንጮ ለታ ትግል ሕይወቱ መጽሐፍን አነበብኩት። መጽሐፉ በ471 ገጾች እና በሦስት ክፍሎች ተቀንብቧል። የመጀመሪያው ክፍል ከልጅነት እስከ ትግል ዋዜማ… Read more: አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱ
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም። ይህ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው







