Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  “ሁሉም ይረዳን  አሳሳቢ ሁኔታ ውስጥ ነን” የራያ ነዋሪዎች ጩኸት “በአላማጣ ከተማም በሌሊት የተደራጀ ዘረፋ እየተካሄደ ነው”
News

“ሁሉም ይረዳን  አሳሳቢ ሁኔታ ውስጥ ነን” የራያ ነዋሪዎች ጩኸት “በአላማጣ ከተማም በሌሊት የተደራጀ ዘረፋ እየተካሄደ ነው”

Ethioreview newsEthioreview news—May 27, 2024
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የሕወሓት ታጣቂዎች ሀብት ንብረት እየዘረፉ ወደ ትግራይ እየጫኑ ነው

በአማራ ክልል በሰሜን ወሎ ዞን የራያ ነዋሪዎች በሕወሓት ዳግም ወረራ ከተፈጸመባቸው ሰነባብተዋል፡፡ ሕወሓት የሰላም ስምምነቱን ሙሉ ለሙሉ አፍርሶ በአማራ ክልል ወረራ መፈጸሙን የአማራ ክልል መንግሥት ማስታወቁ ይታወሳል፡፡ መንግሥት ታጣቂዎች በወረራ ከያዙት አካባቢ ለቀው እንዲወጡም አሳስቦ ነበር፡፡ ነገር ግን አሁንም የሕወሓት ታጣቂዎች የአካባቢውን ማኅበረሰብ ስቃዩን እያበዙበት መኾናቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ በወረራው ምክንያትም ብዙዎቸ ተፈናቅለዋል፤ ሃብት እና ንብረታቸውንም አጥተዋል፡፡

ለደኅንነታቸው ሲባል ስማቸውን የተውነው የአላማጣ ከተማ ነዋሪ በአላማጣ ገጠር ዙሪያ ባሉ አካባቢዎች የሕወሓት ታጣቂዎች ሀብት ንብረት እየዘረፉ ወደ ትግራይ እየጫኑ ነው ይላሉ፡፡ አርሶ አደሮች እርሻ በሚያርሱበት በዚህ ወቅት ከቀያቸው እየተፈናቀሉ በመከራ ውስጥ ናቸው ይላሉ፡፡

በአላማጣ ከተማም በሌሊት የተደራጀ ዘረፋ እንደሚፈጽሙ አንስተዋል፡፡ ማኅበረሰቡ በአስቸጋሪ የደኅንነት ስጋት ውስጥ እንደኾነም ገልጸዋል፡፡ የሕወሓት ታጣቂዎች በአካባቢው ከዛሬ ነገ ይወጣሉ እየተባለ ለሕዝብ ቢነገርም እስካሁን ድረስ እየዘረፉ፣ እያወደሙ፣ ማኅበረሰብ እያሰቃዩ እና እያፈናቀሉ ተቀምጠዋል ነው የሚሉት፡፡

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

ሁሉም ሊረዳን የምንፈልገው አሳሳቢ ሁኔታ ውስጥ ነን ብለዋል፡፡ የእኛ ፍላጎታችን ማንነታችን ተከብሮ፣ ሰላም ተረጋግጦ፣ በሰላም እየሠሩ መኖር ነው፤ የራያ ሕዝብ ነጻነት ይፈልጋል፤ መንግሥት ስጋት የኾኑንን አካላት እንዲያስወጣልን እንጠይቃለን፤ የራያ ሕዝብ የሚፈልገው ማንነቱ ተረጋግጦለት መኖር ነው፣ መንግሥት የሰላም ስምምነቱን ባለው ልክ እንዲፈጸም እንፈልጋለን ብለዋል፡፡

የራያ ሕዝብ አማራነቱን ይዞ፣ በኢትዮጵያዊነቱ ጸንቶ ለመኖር ነው ፍላጎቱ፤ መላው ኢትዮጵያውያን፣ መላው የዓለም ማኅበረሰብ ጥያቄያችን እንዲያውቅልን፣ በደላችን እንዲረዳልን እንፈልጋለን ነው ያሉት፡፡ ሁሉም ከራያ ጎን ሕዝብ ጎን እንዲቆምም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ሌላኛው የአላማጣ ከተማ ነዋሪ በገጠር አካባቢ ያለው ማኅበረሰብ ግፍና በደል እየደረሰበት ነው፤ ሰበቦች እየተፈለጉ ሃብት እየተዘረፈ ነው፤ ነዋሪዎች እየተደበደቡ ላም እና በሬዎቻቸው እየተነዱ እየታረዱ ነው፤ አማራ ነን ስላልን ብቻ ግፍ እየተፈጸመብን ነው ይላሉ፡፡ ወደ ከተማ የገቡት ታጣቂዎች ደግሞ ቀን ቀን መሳሪያቸውን ደብቀው በከተማዋ ሲዘዋወሩ ይውላሉ፤ ሌሊት መሳሪያቸውን አንስተው ሲዘርፉ፣ ሲያወድሙ ያድራሉ ነው ያሉት፡፡ ሐሰተኛ መታወቂያ እየተሰጣቸው ሕገወጥ ሰዎች አካባቢውን ወረውታልም ብለዋል፡፡

በራያ ውስጥ የአማራ ማንነት መገለጫዎች የኾኑ ምልክቶች እና ለታሪክ የሚቀመጡ ማንኛውንም ጉዳዮች እያፈረሱ ነውም ይላሉ፡፡

የራያ ሕዝብ በማንነቱ አይደራደርም፣ ማንነቴን ያስመልስልኛል ብሎ መንግሥትን አምኖ ተቀምጧል፤ ከሕወሓት ቡድን ነጻ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ የማንነቱ ጥያቄ በሕግ እንዲጸድቅለት ፍላጎቱን በተደጋጋሚ በሰላማዊ ሰልፎች ጠይቋል፤ ይሁን እንጅ ዳግም ወረራ ተፈጽሞበት በደኅንነት ስጋት ውስጥ ይገኛል ብለዋል፡፡

መንግሥት የራያን ሕዝብ ፍላጎት ያውቃል፤ ሕወሓትም የራያ ሕዝብ እንደማይፈልገው ጠንቅቆ ያውቃል፤ የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይሄን ተረድቶ ለራያ ሕዝብ ፍትሕ እንዲሰጠው ከጎኑ ሊቆም ይገባል ነው ያሉት፡፡

የራያ ሕዝብ ማንኛውንም ችግር ደም አፋሳሽ ባልኾነ መንገድ፤ ወንድማማችነትን እና ዘላቂ አብሮነትን መሠረት ባደረገ መልኩ ችግሮቹ እንዲፈቱ ፍላጎቱ ነው፤ ተፈናቃይ የሚባሉ ሰዎች ተመልሰው ሕይወታቸውን እየመሩ ነው የነበረው፣ አሁን ግን ተረጋግቶ ሲኖር የነበረውን፣ ሰፊውን እና እውነተኛውን የአካባቢው ማኀበረሰብ አፈናቅለው አዲስ ሰው እያመጡ ነው፣ እውነተኛውን አፈናቅሎ የሚመጣ ሰላም የለም ብለዋል፡፡

በሕገወጥ መንገድ ወደ አካባቢው የገቡ ታጣቂዎች ተመልሰው ሕጋዊ የኾነው ማኅበረሰብ ወደ ቤቱ ተመልሶ ሰላማዊ ኑሮውን እንዲኖር መንግሥት መሥራት ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡ የሕወሓት ታጣቂዎች እየቀረበላቸው ያለውን የሰላም ጥሪ እያከበሩ አይደለም፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ የታጠቀ ኀይል እያሰፉ፣ አካባቢውንም እየወረሩ ነው ብለዋል፡፡ በሚሊዮን የሚገመቱ የማይታወቁ የትግራይ ነዋሪዎችን ሐሰተኛ መታወቂያዎችን እየሰጡ እያስገቡ ነው፤ ወደ ራያ እየገቡ ያሉት ራያን አይተውት የማያውቁ አዲስ ሰፋሪዎች ናቸው ይላሉ፡፡

የሰሜን ወሎ ዞን ምክትል አሥተዳደሪ እና የንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኀላፊ ታምራት ንጋቱ በዞኑ ሥር በሚተዳደሩ ሦስት የራያ ወረዳዎች ላይ ሕወሓት ወረራ ፈጽሞባቸዋል ብለዋል፡፡ በወረራው ምክንያት ቁጥራቸው በርከት ያሉ የኅብረሰተብ ክፍሎች ተፈናቅለዋል፤ በአካባቢው ይሰጡ የነበሩ ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ አገልግሎቶች በሙሉ ተቋርጠዋል፤ ማኅበረሰቡም ለዳግም እንግልት እና ስቃይ ተጋልጧል ነው ያሉት፡፡

የተፈጸመው ወረራ ከሕግና ከሥርዓት ውጭ በመኾኑ አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ በመንግሥት ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያዎች ተሰጥተዋል፤ ነገር ግን የትግራይ ወራሪ ኀይሎች አካባቢውን ተቆጣጥረው በመያዝ በማኅበረሰቡ ላይ ሰፊ እንግልት እየፈጸሙ ነው፤ ይባስ ብሎ ወረራውን እያሰፉ ነው ብለዋል፡፡

የራያ ሕዝብ ለዓመታት ማንነታችን አማራ ነው በማለት ጽኑ አቋም ይዞ ሲታገል ኖሯል፤ ማንነት በምንም መልኩ ሊቀየር አይችልም፣ የትኛውም አይነት ፖለቲካ ቢሠራ እውነተኛውን ማንነት መቀየር እንደማይቻል ሲያሳይ ኖሯል ነው ያሉት፡፡

የሕወሓት ወራሪ የራያን እውነታ በኀይል ልደፍጥጥ በሚል ነው ወረራ የፈጸመው ብለዋል፡፡ ከጦርነት ያገኘነው ጥቅም የለም፤ ማንነትን በጉልበት መደፍጠጥ አይቻልም፤ ማንነትን መደፍጠጥ እንደማይቻል የአካባቢው ማኅበረሰብም የመንግሥት አቋምም ነው ይላሉ፡፡ ጉዳዩን በሰላማዊ መንገድ መፍታት ሲቻል አሁንም በኀይል አሥተዳድራለሁ የሚል ግትር አቋም ያለው ኀይል በሕዝባችን ላይ እየፈጸመው ያለው ድርጊት አሰቃቂ ነው፤ ችግሩን ለመቀልበስ ሰላማዊ አማራጮችን በመጠቀም ጥረት እያደረግን ነው ብለዋል፡፡

የራያ ሕዝብ ጉዳዩ በሰላም ማለቅ አለበት የሚል ጽኑ አቋም ስላለው ያን እየጠበቀ ነው፤ ነገር ግን ይሄን እንደፍርሃት የቆጠረው ወራሪ ኀይል በሕዝብ ላይ በደል እየፈጸመ መኾኑን ገልጸዋል፡፡

የራያ ሕዝብ ለዓመታት ባደረገው ተጋድሎ እና መስዋዕትነት ነጻ ወጥቷል ያሉት ምክትል አሥተዳደሪው ባለፉት ዓመታትም በነጻነት ራሱን በራሱ ሲያሥተዳድር ቆይቷል፤ አሁን ግን በነጻነት ራሱን በራሱ የማሥተዳደር መብቱን እንዳያስቀጥል ወራሪ ኀይሎች መሰናክል ኾነውበታል ብለዋል፡፡

የአካባቢው ማኅበረሰብ ለባርነት፣ ለጭቆና እና ለእንግልት የሚዳርገውን የትኛውንም ኀይል አንቀብልም፤ መንግሥት ሊደርስልን ይገባል እያለ መኾኑንም አንስተዋል፡፡

መንግሥት ለተፋናቃይ ወገኖች የሰብዓዊ ድጋፍ እያደረገ መኾኑንም ገልጸዋል፡፡ነገር ግን እየተደረገ ያለው ድጋፍ በቂ አይደለም ነው ያሉት፡፡

መንግሥት ዘላቂ በኾነ መንገድ የአካባቢውን ጥያቄ ለመመለስ፤ ሕዝብንም ከእንግልት ለመታደግ እየሠራ ነው፡፡ የራያ አማራ ማንነትን በኀይል መውሰድ አይቻልም፤ የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም ለማንነቱ ዋጋ እየከፈለ ያለውን ማኅበረሰብ ሊደግፈው ይገባዋል ብለዋል፡፡

ከትግራይ ጊዜያዊ አሥተዳደር በተደጋጋሚ የሚሰጡት መግለጫዎች እና ራያን በተመለከተ የሚሰጡ ሃሳቦች ፍጹም ተቀባይነት የሌላቸው ናቸው፤ የትግራይ ሕዝብ እንዲህ አይነቱን ጸብ አጫሪ አካሄድ በቃ ሊል ይገባዋል ነው ያሉት፡፡ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አሥተዳደሩም ቆም ብሎ ሊያስብበት እንደሚገባ ነው የገለጹት፡፡

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
የትግራይ ሃይሎች አላማጣ ከተማዋን ለመቆጣጠር ሰፊ ሃይል እያስገቡ ነው፤ ጌታቸው ረዳ አካባቢውን ለቀን ወጥተናል አሉ
በእነ ቀሲስ በላይ መኮንን የክስ መቃወሚያ ብይን ተሰጠ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2