በፎቶው የምናያቸው ጄኔቫ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ሰራተኞች ናቸው። ይህን ፎቶ የተነሱት በዘመነ ደረግ በጄኔቫ የኢትዮጵያ አምባሳደር የነበሩት ከሳ ከበደ ለኢትዮጵያ አምባሳደሮች መኖሪያ እንዲሆን በጄኔቫ ከተባበሩት መንግሥታት ቢሮ በቅርብ ርቀት ላይ በዘመነ ደርግ የገዙት ትልቅ ቪላ ያለው ሰፊ ግቢ ውስጥ ነው።
አምባሳደር ካሳ ከበደ ይሄንን ቤት ሲገዙ ከኢትዮጵያ ሕዝብ በተዘረፈ ገንዘብ መንግሥቱ ኃይለማርያም ሥልጣኑን ሲያጣ በስደት የሚጠለልበት ቪላ በሥሙ ገዙለት ተብለው በወቅቱ የተቃዋሚ ሬድዮ ጣቢያዎች በቪኦኤና መሰል ትላልቅ ተቋማት ጭምር የሥም ማጥፋት ዘመቻ ተከፍቶባቸው ነበር።
በወቅቱ ቪኦኤ ላይ ጭምር ቀርበው ቤቱ የተገዛው ኢትዮጵያ ለአምባሳደሮች መኖሪያ ቤት ኪራይ የምታወጣውን ወጪ ለማስቀረት እና ዶላር ለመቆጠብ መሆኑን እና ንብረትነቱም የኢትዮጵያ መንግሥት እንጂ በመንግሥቱም ሆነ በሌላ ግለሰብ ሥም የተገዛ አለመሆኑን ለማስረዳት ብዙ ቢጣጣሩም በተቃዋሚ ፕሮፓጋንዳ ተደፍቀው ሰሚ አላገኙም ነበር።
እነሆ ዛሬ ታሪክ የሳቸውን ዕውነት እና የተቃዋሚ ፕሮፓጋንዲስቶችን ቅጥፈት መስክራለች ። ዛሬ ላይ ይህ ቤት በወቅቱ የተገዛበትን ዋጋ ብዙ ዕጥፍ የሚያወጣ ዋጋ ሲኖረው ላለፉት 35 ዓመታት ኢትዮጵያ ለአምባሳደሮች መኖሪያ ታወጣ የነበረውን በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላርም ማዳን ችሏል።
እነዚህ የኤምባሲ ሰራተኞች ይህን ፎቶ የተነሱት ዛሬ በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኝ የመትከልን ሀገራዊ ዘመቻ በመደገፍ በዚህ የአምባሳደሩ ግቢ የችግኝ ተከላ አካሂደው ከጨረሱ በሁዋላ ነው።
የምትሰራው ነገር ለሀገር እንደሚጠቅም እርግጠኛ ከሆንክ ወቅታዊ የመንጋ ጩኸት ሳይበግርህ አድርገው።
ዳኛው ጊዜ፣ ዳኛው ታሪክ፣ ዳኛው የነገ ትውልድ !!
via, አብነት

