Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  law  በሙስና የተከሰሱት የብ.መረጃና ደህንነት አገልግሎት ሰራተኞች በስር ፍርድ ቤት የተጣለባቸው የቅጣት ውሳኔ ተሽሮ አዲስ ፍርድ ተፈረደባቸው
law

በሙስና የተከሰሱት የብ.መረጃና ደህንነት አገልግሎት ሰራተኞች በስር ፍርድ ቤት የተጣለባቸው የቅጣት ውሳኔ ተሽሮ አዲስ ፍርድ ተፈረደባቸው

Ethioreview newsEthioreview news—October 16, 2024
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ሰራተኞች በተከሰሱበት ከሲሚንቶ ግዢ ጋር የተያያዘ የሙስና ወንጀል በስር ፍርድ ቤት የተጣለባቸው የቅጣት ውሳኔ ተሻረ።

ተከሳሾቹ ላይ በስር ፍርድ ቤት ተወስኖ በነበረው የቅጣት ውሳኔ ቅር በመሰኘት ዐቃቤ ሕግ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ባቀረበው ይግባኝ አቤቱታ መነሻ መሰረት ተመርምሮ የስር ፍርድ ቤት ውሳኔ ተሽሮ ተሻሽሎ ቅጣት ተጥሎባቸዋል።

የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ስም 29 ሺህ 200 ኩንታል ሲሚንቶ ከሁለት ፋብሪካዎች ገዝተው ለግለሰቦች በመሸጥ በመንግስት ላይ ከ30 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት ደርሷል በማለት የአገልግሎቱ የኮንስትራክሽን እና ሎጂስቲክስ ም/ዳይሬክተርን ጨምሮ በአራት ሰራተኞች ላይ ታህሳስ 3 ቀን 2015 ዓ.ም በዋለው ችሎት በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ መስርቶባቸው ነበር።

በአጠቃላይ ተከሳሾች በጥቅም በመመሳጠር ምንም አይነት የግዢ ፍላጎት ሳይኖር በአገልግሎቱ ስም በፃፏቸው ደብዳቤዎች ከዳንጎቴ እና ደርባ ሲሚንቶ ፋብሪካዎች በድምሩ 29 ሺህ 200 ኩንታል ሲሚንቶ በመግዛት ወደ ተቋሙ ገቢ ሳያደርጉ ገበያ ላይ በመሸጥ 30 ሚሊየን 99 ሺህ 360 ብር ጥቅም ያገኙ መሆኑን ጠቀሶ ነበር ዐቃቤ ሕግ ክስ ያቀረበው።

More stories

ግማሽ ሚሊየን ብር በጥሬው ሲቀበል እጅ ከፍንጅ የተያዘው ተከሳሽ በፅኑ እስራት ተቀጣ

February 1, 2022

ዐቃቤ ህግ በቀድሞ የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት የክስ መዝገብ ሌሎች ድርጅቶችን አካቶ ለመቅረብ ጠየቀ

July 7, 2023

በሰሜን ኢትዮጵያ ባለው ግጭት የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ለመመርመር የተቋቋመው የሚኒስቴሮች ግብረ-ሀይል ስራውን በይፋ ጀምሯል

November 29, 2021

ሰው በማገት ወንጀል የተከሰሱ ሁለት ግለሰቦች 22 ዓመት ከ6 ወር ፅኑ እስራት ተፈረደባቸው

February 16, 2022

ተከሳሾቹ ክሱ ከደረሳቸውና በንባብ ከተሰማ በኋላ ወንጀሉን አልፈጸምንም ሲሉ የሰጡትን የዕምነት ክህደት ቃል ተከትሎ ዐቃቤ ሕግ ለወንጀሉ መፈጸም ያስረዱልኛል ያላቸውን ሶስት ምስክሮችን እና በተያያዥ የሰነድ ማስረጃዎችንም አቅርቧል።

የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት የምስክር ቃል መርምሮ ተከሳሾቹ በተከሰሱበት አንቀጽ እንዲከላከሉ ብይን ሰጥቶ ነበር።

ሆኖም ተከሳሾቹ በተለያዩ ቀናቶች ያቀረቡትን የመከላከያ ማስረጃ የመረመረው ፍርድ ቤቱ 1ኛ ተከሳሽን የብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ተቋም የኮንስትራክሽን እና ሎጂስቲክስ ም/ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ደሜ፣ በተቋሙ የግዢ ባለሙያ ናቸው የተባሉ ቱጅባ ቀልቤሳ እና ሙስጠፋ ሙሳን በተከሰሱበት ድንጋጌ ንዑስ አንቀጽ 1 መሰረት ጥፋተኛ ብሏቸዋል።

ከተሳሾቹ ጋር ቀደም ብሎ ክስ ቀርቦባቸው የነበረና ከዚህ በፊት በነበረ ቀጠሮ በችሎቱ እንዲከላከሉ ብይን ተሰጥቶ የነበረው በተቋሙ የኮንስትራክሽን እና ሎጂስቲክስ ግዢ ፋይናንስ ክፍል ኃላፊ አቶ አሸናፊ ተስፋዬ የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው ተከላክለዋል በማለት በነጻ አሰናብቷቸዋል።

ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት ማቅለያና ማክበጃ አስተያየቶችን መርምሮ ተከሳሾቹ ጥፋተኛ በተባሉበት አንቀጽ 1ኛ ተከሳሽን በ2 አመት ከ6 ወር ጽኑ እስራት እንዲቀጡ የወሰነ ሲሆን÷ ቀሪ ተከሳሾችን ደግሞ 1 አመት ከ6 ወር እስራት እንዲቀጡ ወስኖባቸው ነበር።

ከሁለት ፋብሪካዎች ያለአግባብ በተፈጸመ የ29 ሺህ 200 ኩንታል ሲሚንቶ ግዢ ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በመንግስት ላይ ጉዳት ደርሷል ብሎ ክስ ያቀረበ ቢሆንም ችሎቱ ግን ጥቅም አግኝተውበታል በሚል ለቅጣት ዓላማ የወሰደው እያንዳንዳቸው የ700 ሺህ ብር ጥቅም አግኝተዋል የሚለውን የገንዘብ መጠንን ብቻ ነበር።

በዚህ መልኩ በስር ፍርድ ቤት በተሰጠው የቅጣት ውሳኔን በሚመለከት ዐቃቤ ሕግ በተጣለው ቅጣት ተገቢ ያልሆነና አነስተኛ ቅጣት መሆኑን ጠቅሶ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድቤት 1ኛ ይግባኝ ሰሚ ችሎት ይግባኝ ብሎ ነበር።

ይግባኝ ሰሚ ችሎቱ የዐቃቤ ሕግ የይግባኝ አቤቱታውን ያስቀርባል በማለት በይግባኝ ባይና በመልስ ሰጪ መካከል የቀረበውን የመልስ መልስ እና የግራ ቀኝ ክርክርን መርምሮ በሰጠው ውሳኔ ቀደም ሲል የስር ፍርድ ቤት የጣለውን ቅጣት ውሳኔ ከቅጣት አወሳሰን መመሪያ አንጻር ተሽሮ ተሻሽሎ ቅጣት መጣል እንዳለበት በማመን በስር ፍርድ ቤት የተሰጠው የቅጣት ውሳኔን ሽሮ አሻሽሎ በተከሳሾቹ ላይ የቅጣት ውሳኔ ሰጥቷል።

ይግባኝ ሰሚ ችሎት ቅጣቱን በማሻሻል 1ኛ ተከሳሸ ተስፋዬ ደሜን 5 ዓመት ከ 6 ወር እና በ5 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲቀጣ የወሰነ ሲሆን፣ 2ኛ ተከሳሸ ቱጅባ ቀልቤሳ እና 3ኛ ተከሳሸ ሙስጠፋ ሙሳን ደግሞ በ4 ዓመት ከ5 ወር ጽኑ እስራት እና በ2ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል።

law
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
“ኢሱ ጭሱ”ን ምን እስቀየምናቸው?!
የተሸጡት አባት አባ መፍቀሬ ሰብዕ-    ወደ ፈጣሪያቸው ሄዱ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
law

ህገወጥ የውጭ ምንዛሪ ወንጀል የፈጸሙ 123 ተጠርጣሪዎች የባንክ ሒሳብ ታገደ

September 20, 2025
law

እነ ቀሲስ በላይ በሙስና ወንጀል ሊፈርድባቸው እንደማይገባ ጠቅሰው ያቀረቡት ይግባኝ ውድቅ ሆነ

July 26, 2025
law

የአዲስ አበባ የከንቲባ ፅ.ቤት ፕሮቶኮልን ጨምሮ 12 ተከሳሾች በሌብነት ተከሰው ተፈረደባቸው

July 23, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • INTERVIEW
    • law
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • ያበደው
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2