Skip to content
VOE
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ሔማን በቀለ – ታይም መፅሄት የዓመቱ ምርጥ ያለው ህልመኛ ታዳጊ ሳይንቲስት

    September 4, 2024

    በዩክሬን በኩል ወደ አውሮፓ የሚደርሰው የሩሲያ የተፈጥሮ ጋዝ  ስራው እንዲቆም ተደረገ

    January 1, 2025

    በኦሮሚያ ክልል ማን፣ ምን ፈጸመ? የኢሰመኮ ሪፖርት

    August 5, 2025

    በኦሮሚያ በሌብነት ጉዳይ አናቱ ተፈርቷል፤ በ289 ሺህ ካሬ.ሜ.መሬት ላይ ማጣራት ተጀምሯል

    December 3, 2022

    የአፋር ክልል ከ፴ ዓመታት በሁዋላ በትግራይ ክልል የተወሰደበትን ኣንድ ቀበሌ “ነጻ አ ወጣሁ” አለ

    June 7, 2021
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  SOCIETY  በሳዑዲ ሞት የተፈረደባቸው ኢትዮጵያውያን መንግሥት ሕይወታቸውን እንዲያተርፍ ተማጸኑ
SOCIETY

በሳዑዲ ሞት የተፈረደባቸው ኢትዮጵያውያን መንግሥት ሕይወታቸውን እንዲያተርፍ ተማጸኑ

Ethioreview newsEthioreview news—October 11, 2024
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በደቡባዊ ሳዑዲ አረቢያ ናጅራን እስር ቤት የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የኢትዮጵያ መንግሥት ጣልቃ ገብቶ ሕይወታቸውን እንዲያተርፍ ተማጸኑ።

በእስር ቤቱ እስካሁን ሁለት ኢትዮጵያውያን በሳዑዲ ኃይሎች እንደተገደሉ እና ሌሎቹም ሞታቸውን እየተጠባበቁ መሆኑን የሞት የተፈረደባቸው ሁለት ስደተኞች ለቢቢሲ ገልጸዋል።

እነዚህ በእስር ላይ ያሉ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ወደ 47 እንደሚሆኑ እነኚሁ ስደተኞች ከቢቢሲ ጋር ባደረጉት የስልክ ቆይታ አስረድተዋል።

“መቼ እንደምንሞት ባናውቅም ሞት ተፈርዶብናል። ዛሬ ልንገደል እንችላለን ወይም ነገ፤ አናውቅም። በጣም ፈርተናል። ለምን ሞት እንደተፈረደብኝ አላውቅም። ድንበር በሕገ ወጥ መንገድ አልፈሃል ነው የተባልኩት። ከታሰርኩ አምስት ዓመት ከአምስት ወር ሆነኝ” ሲሉ እኚህ ስደተኛ ለቢቢሲ ያደረባቸውን ከፍተኛ ፍርሃት በስልክ ገልጸዋል።

More stories

በላልይበላ የሽብር ቡድኑን ጭካኔ ተጋፍጦ አገልግሎት!

December 29, 2021

መታወቂያዎን ከብጉር፣ ከማድያትና መቃጠል እየተከላከሉት ነው?

May 4, 2025

በሶማሌ ክልል በተከሰተው የጎርፍ አደጋ 28 ሰዎች ሲሞቱ ከ300,000 በላይ ሰዎች ተፈናቅለዋል

November 20, 2023

ጥንቃቄን የሚሻው የስኳር ህመም

November 24, 2024

የሞት ፍርድ ሲፈረድባቸው እውነት ይሆናል ብለው እንዳላሰቡ ለቢቢሲ የተናገሩት ኢትዮጵያዊው ስደተኛ እስረኛ ባለፈው ሳምንት ሁለት ኢትዮጵያውያን እስረኞች መገደላቸውን ተከትሎ “የእኛም ዕእጣ ፈንታ ሞት እንደሆነ አወቅን” ይላሉ።

“በሞት እና በሕይወት መካከል ነው ያለነው። ሌሎቹ ከተገደሉ በኋላ መተኛት አልቻልንም” ሲሉ ተናግረው “መንግሥታችን ጉዳዩን እንዲሰማልን እንፈልጋለን” ሲሉ ተማጽነዋል።

አክለውም በእስር ላይ ስላሉት ኢትዮጵያውያን ባሳዑዲ አረቢያ የሚገኘው “ኤምባሲ መጥቶ ጠይቆን አያውቅም” ሲሉ ተናግረዋል።

በእስር ቤቱ እያሉ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው ሌላኛው ኢትዮጵያዊ ስደተኛ በበኩላቸው “እዚህ እስር ቤት ያለው ስሜት አስጨናቂ ነው። ፈርተናል። ፖሊስ ወደ እስር ቤት ወረቀት ይዞ በመጣ ቁጥር የሚገደል ሰው ሊወስድ ነው ብለን እንፈራለን። ጠዋትም ማታም ሲመጡ እንደነግጣለን። አሁን ሞትን እየጠበቅን ነው። ምንም ማድረግ አንችልም። ሞታችን የማይቀር ነው” ሲሉ በከፍተኛ ሐዘን ተናግረዋል።

በርካታዎቹ ሞት የተፈረደባቸው ግለሰቦች ያለ ጥፋታቸው እንደሆነ የሚናገሩት ስደተኛ እስረኛው የኢትዮጵያ መንግሥት ከሳዑዲ መንግሥት ጋር ተነጋግሮ ሕይወታቸውን እንዲታደጋት ተማጽነዋል።

ስደተኛው ኢትዮጵያ ወዳሉ ቤተሰቦቻቸው ደውለው የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት ከሳዑዲ መንግሥት ጋር እንዲነጋገሩ ጥያቄ እንዲያቀርቡ መናገራቸውን ገልጸዋል።

“ወደ አገር ቤት ደውለን ቤተሰቦቻችን መንግሥት ጋር ሄደው ከሳዑዲ መንግሥት ጋር እንዲያወሩ ጠይቀውልን ነበር። እንደሚነጋገሩ ቃል ሲገቡላቸው ቤተሰቦቻችን ተመለሱ። መፍትሄ እንደምናገኝ ለቤተሰቦቻን ቃል ቢገባላቸውም እኛ ግን መፍትሄ አላገኘንም” ብለዋል።

አክለውም “ብዙ ሰዎች ሞት ተፈርዶባቸዋል። እስካሁን ሁለቱ ተገድለዋል።. . . አደንዛዥ ዕጽ አስገብታችኋል ተብለው ነው የተከሰሱት። የኢትዮጵያ መንግሥት ጣልቃ ገብቶ ከሳዑዲ መንግሥት ጋር ተነጋግሮ ያድነን። የተከሰሱት በሐሰት ነው። ያለ ጥፋት ነው እየተገደሉ ያሉት” ሲሉ ለቢቢሲ ገልጸዋል።

በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ የሞት ቅጣት መፈጸም እንደ አዲስ የተጀመረ እንደሆኑ የገለጹት ስደተኞቹ ከዚህ ቀደም የሞት ፍርድ ተፈጻሚ የሚሆነው በሰው ግድያ ወንጀል የተከሰሱ ናቸው ይላሉ።

ቢቢሲ ኢትዮጵያውያኑ በምን ዓይነት ወንጀል ተከሰው ሞት እንደተፈረደባቸው ከእስር ቤቱ ባለሥልጣናት ማረጋገጥ አልቻለም።

በሳዑዲ አረቢያ ከአደንዛዥ ዕጽ ጋር በተያያዘ በእስር ቤቶች የሚፈጸሙ ግድያዎች በከፍተኛ ሁኔታ ማሻቀቡ ስጋት እንደፈጠረባቸው የሰብዓዊ መብት ተቋማት በያዝነው ዓመት መስከረም ወር ላይ የካይሮ ኢንስቲትዩት ፎር ሂውማን ራይት ስተዲስ ድረ ገጽ ላይ በወጣ ጥሪ አስታውቆ ነበር።

ተቋማቱ በሳዑዲ በሚገኘው ታቡክ እስር ቤት በመቶዎች የሚቆጠሩ እስረኞች ሕይወታቸው አደጋ ላይ እንደወደቀ ገልጸው ካለፈው ዓመት ጥር ጀምሮ ስምንት እስረኞች በሞት መቀጣታቸውን ገልጸዋል።

በመላው አገሪቱ ደግሞ 42 ሰዎች ከአደንዛዥ ዕጽ ጋር በተያያዘ የሞት ፍርድ ተፈጻሚ ሆኖባቸዋል ብሏል።

የሰብዓዊ መብት ተቋማቱ የሳዑዲ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴርን ዋቢ አድርገው ባሰፈሩት ጽሁፍ በዚሁ ወቅት ከአደንዛዥ ዕጽ ጋር በተያያዘ የሞት ቅጣት ተፈጻሚ የሆነባቸው ግለሰቦች ዜግነታቸው ከኢትዮጵያ፣ ከግብፅ፣ ከሶሪያ፣ ከሱዳን፣ ከየመን፣ ከናይጄሪያ ይገኙበታል ብለዋል።

ሳዑዲ አረቢያ የሞት ፍርድ የፈረደችባቸውን ግለሰቦች በይፋ ባታሳውቅም ከአደንዛዥ ዕጽ ጋር በተያያዘ ክስ የተመሠረተባቸው በመቶዎች የሚቆጠሩ የተለያዩ ዜግነት ያላቸው እስረኞች አሏት።

ሳዑዲ አረቢያ ከአደንዛዥ ዕጽ ጋር በተያያዘ ክስ የተመሠረተባቸውን ግለሰቦች በሞት መቅጣት በአውሮፓውያኑ 2020 አግዳ ነበር። ከሁለት ዓመታት በፊትም ልዑል አልጋወራሽ ሞሐመድ ቢን ሳልማን የሞት ቅጣት ተፈጻሚነት በግድያ ወንጀል ብቻ እንዲወሰን አውጀው ነበር።

ሆኖም በዚያው ዓመት ከጥቂት ወራት በኋላ ሳዑዲ ምንም ዓይነት ምክንያት ሳትሰጥ ከአደንዛዥ ዕጽ ጋር በተያያዘ የተከሰሱ ግለሰቦች ላይ የሞት ቅጣትን ተፈጻሚ ማድረግ ጀምራለች። የሰብዓዊ መብት ተቋማቱ እንዳሰፈሩት ካለፈው ዓመት ጥር ወር ጀምሮ የሞት ቅጣት 72 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን ጠቅሰዋል።

በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የሞት ፍርድ ተላልፎባቸው መገደላቸውን በተመለከተ መረጃ ካለ በሚል የተለያዩ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶችን ቢቢሲ ቢጠይቅም መረጃ እንዳልደረሳቸው ገልፀዋል።

የኢትዮጵያውያኑን ጉዳይ በተመለከተ ከማክሰኞ መስከረም 28/ 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በስልክ እንዲሁም በጽሑፍ መልዕክት ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

በነዳጅ ምርት የበለጸገችው ሳዑዲ አረቢያ በርካታ ኢትዮጵያውያን ሠርቶ ለመቀየር መዳረሻ ከሚያደርጓቸው የመካከለኛው ምሥራቅ አገራት መካከል አንዷ ነች።

ይሁን እንጂ የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት በተለያየ የወቅት በአገሪቱ የሥራ እና የመኖሪያ ፍቃድ የላቸውም በሚል በርካታ ኢትዮጵያውያን እጅግ አስቸጋሪ በሆኑ እና በማያፈናፍኑ እስር ቤቶች እንደሚቆዩ እንዲሁም ለተለያዩ የጤና እክሎች መጋለጣቸውን ቢቢሲ ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ መዘገቡ ይታወሳል።

እስረኞቹ በቂ ምግብ እና የሕክምና አገልግሎት ማግኘት በማይችሉበት እና በሕይወት ለመቆየት አስቸጋሪ በሆነ ሁኔታ እንደሚያዙ ይናገራሉ።

በማቆያ ማዕከላትም ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በተጨናነቀ ሁኔታ ከመቆያታቸው ባሻገር በጥበቃዎች ማሰቃየት እና ድብደባ እንደሚፈጸምባቸው የመብት ተቆርቋሪው ድርጅቱ ሂዩማን ራይትስ ዋች መግለጹ የሚታወስ ነው።

በዚህም የማዕከሉ ጥበቃዎች በጎማ በተሸፈነ ብረት በፈጸሙባቸው ድብደባ ስደተኞች መሞታቸውንም ተመልክቷል።

በተጨማሪም በጦርነት እየታመሰች ካለችው የመን ወደ ሳዑዲ አረቢያ ድንበር ለማቋረጥ የሞከሩ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ኢትዮጵያውያንን የሳዑዲ ድንበር ጠባቂዎች መግደላቸውን የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ሂማን ራይትስ ዋች ባለፈው ዓመት ሪፖርት ማውጣቱ ይታወሳል።

ሂዩማን ራይትስ ዋች ከመጋቢት 2014 ዓ.ም. እስከ ሐምሌ 2015 ዓ.ም. ድረስ ቢያንስ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በሳዑዲ የድንበር ጠባቂዎች ተገድለዋል ብሏል በሪፖርቱ።

ተቋሙ በመቶዎች የሚቆጠሩ በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ የተፈጸመውን የጅምላ ግድያ በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸም ወንጀል እንደሆነም ባወጣው ዘርዘር ያለ ሪፖርት ጠቅሷል።

ሂውማን ራይትስ ዋች የጅምላ ግድያውን የያዘውን ሪፖርት ‘ዘይ ፋየርድ ኦን አስ ላይክ ሬይን’ [ጥይት እንደ ዝናብ በላያችን ላይ አዘነቡብን] የሚል ርዕስ ሰጥቶታል።

ሪፖርቱ የመን ከሳዑዲ አረቢያ ጋር በምትዋሰንበት ድንበር ላይ የሳዑዲ ፖሊስ እና ወታደሮች ጥይት እና ተቀጣጣይ ፈንጂዎችን ጭምር በመጠቀም በጅምላ በአሰቃቂ ሁኔታ እንደገደሏቸው የስደተኞችን ምስክርነት ይዟል።

በድንበር አካባቢ የበሰበሱ አስከሬኖች፣ በሳዑዲ ድንበር ጠባቂዎች የተያዙ ስደተኞች የትኛው እግራቸው በጥይት እንዲመታ እንዲመርጡ፣ እንዲሁም መትረየስ እና ሌሎች መሳሪያዎች በርካቶችን በጅምላ ለመግደል ጥቅም ላይ መዋላቸውን የሚያሳይ ዘርዘር ያለ ሪፖርት ነው ማዕከሉ ይዞት የወጣው።

የሂዩማን ራይትስ ዋች ሪፖርት ጠለቅ ያለ ሲሆን በርካታ የዓይን እማኞችን ጨምሮ፣ በርካታ ግድያዎች የተፈጸሙባቸውን ስፍራዎች የሚያሳዩ የሳተላይት ምሥሎች እንዲሁም ጊዜያዊ የቀብር ስፍራዎችን ይዟል።

ሪፖርቱ በተጨማሪም ስደተኞች በታጠቁ ሕገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ታጅበው ወደ ድንበር ከመወሰዳቸው በፊት ስለሚታሰሩበት የየመኑ ሞናቢህ የማቆያ ማዕከልም ይጠቅሳል።

ዘገባው የቢቢሲ ነው

SOCIETY
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
አቶ ድንቁ ደያስ ቴሌቪዥን ጣቢያ የሳተላይት ኪራይ ወጪውን መቋቋም ተስኖት ስርጭቱን አቋረጠ
ግብፅ፣ ሶማሊያና ኤርትራ አስመራ ላይ ተስማሙ- ኤርትራ ከኢትዮጵያ ይልቅ ግብጽን መርጣ በገሃድ ዘመቻ ከፈተች
Related posts
  • Related posts
  • More from author
SOCIETY

አስጨናቂዋን ሰዓት ወደ ደስታ የቀየረው የኢትዮጵያዊያን የሕክምና ባለሙያዎች ስኬት

August 23, 2025
News

በ2018 ጓደኞቼ ዩኒቨርስቲ ይገባሉ፤ በድህነት ከተማ ሄዶ መማር ይልቻለው ታዳጊ ለቅሶ!

August 22, 2025
SOCIETY

“በጠለምት ወረዳ በዝናብ እጥረት ሳቢያ እንስሳት እየሞቱ ነው፤ ሕዝብ እየተሰደደ ነው”

August 18, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2