– ወላጆች ለትምህርት ቤቶች ዕድሳት ከ40 ቢሊዮን ብር በላይ በዓይነትና በገንዘብ ድጋፍ አደረጉ
– ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ 30 ሺህ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ተሰርተዋል አሳይቶናል፣
ወላጆች የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል “ትምህርት ለትውልድ” በሚል ሀሳብ ትምህርት ቤቶችን ለማሻሻል በተደረገ ንቅናቄ 40 ቢሊዮን ብር በዓይነትና በገንዘብ ድጋፍ ማድረጋቸውን የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናገሩ።
ወላጆች በትምህርት ውጤት መስተካከል ላይ የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል።
በዚህም 7 ሺህ 500 አዲስ ትምህርት ቤቶች፤ ባለፉት ሁለት አመታት ብቻ 30 ሺህ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ተሰርተዋል፡፡ ነባር 22 ሺህ ትምህርት ቤቶች ተጠግነዋል፡፡ ቤተሰብ ገንዘብ ከማዋጣት አልፎ የልጆቹን የትምህርት ውሎ መከታተል ሲጀምር የተማሪዎች ውጤት የበለጠ እየተሻሻለ ይሄዳል ብለዋል፡፡
ባለፉት ሦስት ዓመታት የተመዘገበው አነስተኛ ውጤት እንደ ሀገር የደረሰንበትን ውድቅት አሳይቶናል፡፡ ውጤቱን የማስተካከል ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ፤ ተማሪዎች ማለፍ የሚቻለው በስራ መሆኑን ሲገነዘቡ ይሰተካከላል።
ትምህርት በአቋራጭና በስርቆት አልፋለው ብሎ በሚያስብ ተማሪና ማህበረሰብ ውስጥ አስተማሪዎችን ብታስተካክል የትም አትደርስም ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ እውነታ ከዚህ የተለየ አለመሆኑን የገለፁት ሚኒስትሩ ባለፈው ዓመት 5 ነጥብ 2 በመቶ ውጤት የተመዘገበ ሲሆን የተወሰነ ለውጥ መጥቷል፡፡
ትምህርት ቤቶች ተማሪዎችን ተጨማሪ ሰዓት የድጋፍ ትምህርት መስጠት በመጀመራቸው የተወሰነ የውጤት መሻሻል ታይቷል፡፡ በስርዓት ማስተማር በመጀመራቸው ያለፈው አመት ውጤት መሻሻል ችሏል ብለዋል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ውጤት ዝቅተኛ የመሆን ምክንያቶችን አስመልክቶ ያጠናውን ጥናት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ማቅረቡ ይታወሳል።
በሞገስ ጸጋዬ (ኢ ፕ ድ)

