Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  POLITICS  በጅቡቲ ኢትዮጵያውያኖች በ3 ቀን ውስጥ ውጡ – ዲፕሎማሲ በአስቸኳይ!
POLITICS

በጅቡቲ ኢትዮጵያውያኖች በ3 ቀን ውስጥ ውጡ – ዲፕሎማሲ በአስቸኳይ!

Ethioreview newsEthioreview news—April 30, 2025
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በጣም ብዙ ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ነው ያለው፣ ከኢትዮጵያዊ ቀጥሎ የመኖች ናቸው፡፡ ግን ሁሌም ውጡ የሚባሉት ኢትዮጵያውያኖች ናቸው፡፡ ምክንያቱን አላውቅም፡፡ በፖሊስ ሁሌም አፈሳ አለ፣ የሚታፈሱት ኢትዮጵውያን ናቸው፡፡ ሌሎች ዜጎች ላይ እንደዛ ሲደረግ አይታይም፡፡ ከዚህ በፊትም እንደዚሁ ሰዎችን የመያዝ፣ የማሰር፣ ገንዘብ ተቀብሎ የመልቀቅ ሁኔታዎች ነበሩ፡፡

” 30 እና 40 አመታት የኖረ፣ ቤት ንብረት ያፈራ፣ ቤተሰብ የመሰረተ ሰው ብዙ ነው፡፡ ኑሮውን ሁሉ በ3 ቀን ውስጥ ማቋረጥ አይችልም ” – በጅቡቲ የሚኖር ኢትዮጵያዊ

የጅቡቲ መንግስት በሀገሩ የሚኖሩ ሰነድ አልባ ኢትዮጵያውያንን በፈቃዳቸው ለቀው እንዲወጡ፣ እንደዛ ካልሆነ ግን የግዳጅ አፈሳ እንደሚጀመር ማስታወቁ ይታወሳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ውሳኔውን አስመልክቶ በጅቡቲ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ምን ላይ ይገኛሉ ሲል የተለያዩ ኢትዮጵያዊያንን አያነጋገረ ይገኛል።

አስተያየታቸውን የሰጡንና የጅቡቲ ነዋሪ የሆኑት ኢትዮጵያዊ አቶ ኑሩ አስፋው መንግስት የዜጎችን ስቃይ ለመቀነስ በዲፕሎማሲያዊ አካሔድ ጣልቃ መግባት አለበት ባይ ናቸው፡፡

እሳቸው በጅቡቲ በህጋዊ መንገድ እየኖሩ መሆናቸውን የጠቀሱት አስተያየት ሰጪው፣ ነገር ግን ህጋዊ ሰነድ የሌላቸው ኢትዮጵያውያን እጅግ በርካቶች እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡ ከዚህ ውስጥ 30 እና 40 አመታት የኖረ፣ ትላልቅ የንግድ ድርጅቶችን የከፈቱ፣ ሀብትና ንብረት ያፈሩ፣ አግብተው የወለዱ ኢትዮጵያውያን አሉ ብለዋል፡፡

” በአሁኑ ጊዜ ህዝቡ በከፍተኛ ግራ መጋባት ውስጥ ነው ያለው፣ በሦስት ቀናት ውስጥ የሚይዘው የሚጨብጠው ነገር የለም ” ብለዋል አቶ ኑሩ፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት በአስቸኳይ ከጅቡቲ መንግስት ጋራ ተነጋግሮ ዜጎቹን ከጭንቀት እንዲታደግም ተማፅነዋል፡፡



አቶ ኑሩ በዝርዝር ምን አሉ ?

” በተገለፀው ማስታወቂያ መሰረት መመዝገብ የጀመሩ አሉ፣ በመኪና መውጣት የጀመሩም አሉ፡፡ ነገር ግን አብዛኛው ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ እያደረገ አይደለም፡፡ አሁን 3 ቀን ብቻ ነው የቀረው፡፡ በአውሮፕላንና በባቡር መውጣት አትችልም፣ ህጋዊ የጉዞ ሰነድ ካልያዝክ፡፡ ከጅቡቲ ውጡ የሚለው ጉዳይ የተሳሳተ ይመስለኛል፡፡

በጣም ብዙ ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ነው ያለው፣ ከኢትዮጵያዊ ቀጥሎ የመኖች ናቸው፡፡ ግን ሁሌም ውጡ የሚባሉት ኢትዮጵያውያኖች ናቸው፡፡ ምክንያቱን አላውቅም፡፡ በፖሊስ ሁሌም አፈሳ አለ፣ የሚታፈሱት ኢትዮጵውያን ናቸው፡፡ ሌሎች ዜጎች ላይ እንደዛ ሲደረግ አይታይም፡፡ ከዚህ በፊትም እንደዚሁ ሰዎችን የመያዝ፣ የማሰር፣ ገንዘብ ተቀብሎ የመልቀቅ ሁኔታዎች ነበሩ፡፡

አንዳንዴ ግጭት በሚፈጠርበት ጊዜ (ኢትዮጵያዊው እርስ በርሱ ይጋጫል አንዳንዴ)፣ ወንጀል በሚፈፀምበት ጊዜ እንደዚህ ውጡ ምናምን ስለሚባል፣ ሰው ትኩረት አልሰጠውም ነበር፡፡ እንደዚህ በይፋ ለቃችሁ ውጡ ተብለን አናውቅም፡፡ በዚህ ምክንያት ችላ ብሎት ተዘናግቷል፡፡ የአሁኑ ለየት የሚያደርገው በመንግስት ደረጃ በይፋ መገለፁ ነው፡፡

ሰው በጣም ተደናግጧል፡፡ ቀነገደቡ ይራዘማል የሚል ተስፋ ነበረው፡፡ አሁን 3 ቀን ቀርቶታል፡፡ መፍትሔ ከመዘየድ ይልቅ ዝም ብሎ መጨነቅ ላይ ነው ያለው ስደተኛው፡፡ የንግድ ተቋማት ያሉዋቸው ሰዎች ብዙ ናቸው፡፡ በ5 ቀን ምን ማድረግ ይችላሉ ? ” ብለዋል።

ንብረት ያፈሩ ሰዎች እንዴት ህጋዊ ሰነድ የላቸውም ?

አቶ ኑሩ ለዚህ ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡ ” ሰው ጅቡቲ ሀገሬ ናት ብሎ ነው እስካሁን የሚያስበው፡፡ እንዲህ አይነት ነገር ይመጣል ብሎ አያስብም፡፡ ኢትዮጵያና ጅቡቲ እንደ አንድ ሀገር ነው የሚታሰቡት፡፡

ራሳቸው ጅቡቲዎችም እንደዛ ነው የሚሉት፣ አሁንም በመንግስታቸው ውሳኔ ደስተኞች አይደሉም፡፡ በዚህ ተዘናግተው ነው ለአመታት ያለ ህጋዊ ሰነድ የሚኖሩት፡፡ ጅቡቲንና ኢትዮጵያን ለያይቶ ማየት አይቻልም፡፡ ” ብለዋል

አክለውም ” ለሚባረሩት ዜጎች መንግስት ሊደርስላቸው ይገባል ” ሲሉ ተማጽነዋል።

” እዚህ ያለው ህዝብ ንብረቱን ሸጦ፣ በራሱ ተመዝግቦ፣ ተረጋግቶ የሚወጣበት እድል ሊመቻችትለት ይገባል፡፡ በ3 ቀን ውስጥ ለቃችሁ ውጡ ማለት አግባብ አይደለም፡፡

በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዜጎችን ስቃይ የሚቀንስበትን መንገድ ማመቻቸት አለባቸው፡፡ ወደ ሀገራቸው ከተመለሱም በኋላ የሚቋቋሙበት ዕድል መመቻቸት አለበት፡፡

አፈሳ ከተጀመረ አደገኛ ነገር ነው፡፡ ተይዘህ ወደ ማቆያ ትገባለህ፣ ከዛም በግድ ተጭነህ ትባረራለህ፡፡ ንብረት አትይዝም፣ ገንዘብህን አትሰበስብም፣ ቤተሰቦችህን የመሰናበት ዕድል አይኖርህም፡፡ ካለህበት ሁሉ ተለቅመህ ነው የምትወሰደው፡፡

የቤት ሰራተኞች አሉ፣ ደመወዛቸውን እንኳን በወቅቱ አይሰጡዋቸውም፣ ደመወዝ ሳይዙ ሊባረሩ ነው ማለት ነው፡፡ መንግስት እንዲደርስላቸው ነው የምማፀነው፡፡ ” ሲሉ ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትጵያ

POLITICS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
የቤት ውስጥ ባሪያው ማን ነው?
የውጭ ባሪያውስ…?
ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ተአቅበው እንዲቆዩ ቋሚ ሲኖዶስ ወሳኔ አሳለፈ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
POLITICS

ኢራን እኛ ላይ ምን ልታደርግ ትችላለች?

March 28, 2026
POLITICS

አስቸኳይ የአርበኛነት ጥሪ ለኢትዮጵያን

March 4, 2026
POLITICS

ትራምፕ ኢራንን እንደሚወጉ ፍንጭ ሰጡ

January 28, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2