Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  “ሾልኮ ወጣ” የተባለው የዝርፊያ ሰነድና ለትግራይ ጊዜያዊ አስተዳር የቀረበ ምላሽ
News

“ሾልኮ ወጣ” የተባለው የዝርፊያ ሰነድና ለትግራይ ጊዜያዊ አስተዳር የቀረበ ምላሽ

Ethioreview newsEthioreview news—May 19, 2025
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

“ሾልኮ የወጣው ሚስጥራዊው ሰነድ ” ተብሎ የተሰራጨው መረጃ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አቶ ጌታቸው በፋና ቴሌቪዥን ቀርበው ላጋለጡት ወንጀል የሰጠውን መልስ ተከትሎ የተሰጠ ይመስላል።

ሪፖርተር ቲዩብ አቶ ገብሩ አስራትን “የድርጅቱን ሚስጢር በዚህ ደረጃ ማጋለጥ…” ብሎ ለተየቃቸው ደብቆ ካልሆነ በስተቀር ከዚህም በላይ ወንጀሎች ስለመፈጸማቸው ጥርጥር እንደሌላቸው ገልጸዋል። አያዘውም ምን አልባትም በመንግስት ሚዲያ ለፕሮፓጋንዳ እንዲውል ማድረጉ ላይ ካልሆነ በስተቀር የትህነግ ሰዎች ሌብነት ሊሸፈን እንደማይችል አመልክተዋል።

አሁን ደርስ የማይታወቁ እስር ቤቶች መኖራቸውን፣ ገዳዮች እንዳሉና በርካታ ወነጀሎች እንደሚፈጸሙ ያመልከቱት አቶ ገብሩ አስራት፣ ትህነግ አሁን ቢሰረዝም ቀድሞ የሞተ ድርጅት መሆኑን ጠቁመዋል። ከዚህ ሾልኮ ወጣ ከተባለው ሰነድ ጋር ተያያዥነት ስላለው የአቶ ገብሩን አስተያየት ቀንጭበን ወሰድን እንጂ ዋናው መነሻ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የከፍተኛ ጦር መኮንኖች ስም ተነሳ በሚል ያወጣው መረጃ ነው።

”  የጊዚያዊ  አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት በመሆናቸው ብቻ ያወቁትን ሚስጥር እሰከ መጨረሻ መጠበቅ ሲገባቸው ለርካሽ ገበያ አቅርበዋል ” ሲል የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ፅ/ቤት አቶ ጌታቸውን ወርፎ መግለጫ ማውጣቱ አይዘነጋም። በዚሁ መግለጫ ላይ ” ጥቂት ወንጀለኞችን ለማዳን ሲባል በህዝብ ስም መነገድ ይቁም ” ሲሉ አቶ ጌታቸው ረዳ ምላሽ ሰጥተዋል።

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚንስትር አቶ ጌታቸው ረዳ በቅርቡ  ፋና ቴሌቪዥን ላይ ቀርበው የተናገሯቸውን ንግግሮች አስመልክቶ የተቃውሞ መግለጫ አውጥተዋል።

በመግለጫው አቶ ጌታቸው ለፋና ቴሌቪዥን የሰጡትን ቃለመጠይቅ ” የህግ ልዕልና ለማረጋገጥ ያለመ ሳይሆን የህዝቡን የትግል ታሪክና ቀጣይነት የሚያጎድፍና የሚያጨልም በቂም በቀል የታጨቀ ነው ” ሲል ገልፆታል። 

” በስልጣን ቆይታቸው የታዩ ወድቀቶች ሙሉ በሙሉ ወደ ሌላ አካል ሲያላክኩና ከሳሽ ሲሆኑ ሰንብተዋል ” ያለው ፅ/ቤቱ ” ይህ ወደ ሚድያ ፕሮፓጋዳ የወረደ ሃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው ” ብሏል።

የፅ/ቤቱ መግለጫ ፤ አቶ ጌታቸው ህገወጥ የሰዎች ዝውውር አስመልክቶ በብዙ ጥረት ተጠንቶ ወደ እጃቸው የገባ ኮፒ ያልተደረገ ሰነድ በወቅቱ ተጠያቂነት ሳያረጋግጡ ቀርተው አሁን በማህበራዊ ሚድያ እንዲሰራጭ አደርገዋል ሲል ይከሳል።

” ይህ ሃላፊነት የጎደለው ተግባር ሊያጠቋቸው የፈለጓቸው ግለሰቦች ላይ ብቻ  ያነጣጠረ ሳይሆን ፍትህና ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ የሚደረገው እንቅስቃሴ የሚጎዳ በጥናቱ ተሳትፎ የነበራቸውና አካላትና ቤተሰቦቻቸው ጭምር ለአደጋ የሚያጋልጥ የነውር ነውር ነው ” ሲል በምሬት ወቅሷል።

” የጊዚያዊ  አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት በመሆናቸው ብቻ ያወቁትን ሚስጥር እንደ አንድ የህዝብ ብሄራዊ ጉዳይ እሰከ መጨረሻ መጠበቅ ሲገባቸው ለርካሽ ገበያ ማቅረባቸው ማንነታቸው ያሳየ ተግባር ነው ” ሲል አቶ ጌታቸው ረዳን ወርፉዋቸዋል።

የፕሬዜዳንት ፅ/ቤቱን መግለጫ ተከትለው ወድያውኑ ምላሽ የሰጡት አቶ ጌታቸው ረዳ ” የተጠናው ጥናት ተንተርሶ ወደ እርምጃ እንደማይገባ ስላወቅኩኝ ወደ ሚመለከተው የበላይ አካል መረጃውን ልኬዋለሁ ” ብለዋል። ስም ባይጠቅሱም ሰነዱን ከፌደራል መንግስት አስረክበዋል። ከትግራይ እንደወጡ አስቀድመው ሰነዱ እጃቸው ላይ እንዳለ ማስታወቃቸው አይዘነጋም።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

አቶ ጌታቸው ” በጥናት ሰነዱ መሰረት ህጋዊ እርምጃ ሊወሰድባቸው ከሚገባ ተጠያቂዎች እንዳንዶቹ ከአገር ወጥተዋል ” ሲሉ ሆን ተብሎ እንዲኮበልሉ መደረጉንም አመልክተዋል።

” ሰው መሸጥ (slave trading in modern parlance  ) ለትግራይ ህዝብ የማይመጥን ወንጀል ነው ‘ የሚል አገላለፅ በፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት የወጣ መግለጫ የለም ” ያሉት አቶ ጌታቸው ” ሰነዱ ግለሰቦችን ከማጥቃት ባለፈ የህግ ልዕልና እንዲረጋገጥ ያለመ ነው ” ሲሉ አብራርተዋል።  

ሚንስትር አቶ ጌታቸው ረዳ ” በጥናት ሰነዱ የተቀመጠው ሃቅ ነው ጥቂት ወንጀለኞች ለማዳን ሲባል በህዝብ ስም መነገድ ይቁም ” ብለዋል። ከሰሞኑን አንድ ሚስጥራዊ ሰነድ ሾልኮ ወጥቶ ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል። በማህበራዊ ሚዲያዎችም በርካቶች እየተቀባበሉት እንደሚገኙ ጠቅሶ ቲክቫህ እንዳተመው ከሆነ ሰነዱ ቁልፍ ጉዳዮችን ይዟል።

ሚስጥራዊ ሰነዱ የህገወጥ የሰዎች ዝውውር (በብዛት ኤርትራውያን በህገ-ወጥ መንገድ ማዘዋወር የሚመለከት) እና ሌሎችም ጉዳዮች ላይ የተጠና ሰነድ ሲሆን በአራት ክፍሎች የተከፋፈሉ 69 ገፆች አሉት።

በሰነዱ በጥናት የተለዩ የወንጀል ተግባራት ፦
– ስልጣን ያለአግባብ በመጠቀም
– በወንጀል የተገኘን ገንዘብ ህጋዊ አስመስሎ በመያዝና በማዘዋወር (መኒ ላውንደሪንግ)
– ሰው ማፈንና መሰወር
– በህገወጥ መንገድ ሰዎችን ከአገር ወደ አገር ማዘዋወር
– የመንግስት ስራ ምቹ ባልሆነ መንገድ መምራት
– ሃላፊነት ባልተገባ መንገድ በመጠቀም
– ሙስና የመሳሰሉት ወንጀሎች መፈፀማቸውን ያረጋግጣል።

በሰነዱ በተጠቀሱ የወንጀል ተግባራት በሰራዊት አመራር ያሉ የነበሩ የጀነራል መዓረግ ካለቸው ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች እስከ ቀበሌ አመራር ያሉ አስተዳዳሪዎች ነጋዴዎችና ሌሎች የሚገኙባቸው 231 ተጠርጣሪዎች በስምና አድራሻቸው ተጠቅሷል።

ሰነዱ በህገ-ወጥ መንገድ የተዘዋወሩ ኤርትራውያን ስም የተዘዋወሩበት ቦታና ቀን ፣ ያረፉባቸው ሆቴሎች እንዲሁም ለህገወጥ ዝውውሩ ገንዘብ ገቢ ያደረጉባቸው የባንክ የሂሳብ ቁጥሮች ሰፍረዋል። የጥናት ሰነዱ የሰው ማስረጃ ፣ የድምፅ ቅጂ፣ እንዲሁም በድብቅ የተቀረፀ ምስል ያካተተ እንደሆነ ይዘረዝራል።

በሰነዱ በቀንደኛ ተጠርጣሪነት ከተጠቀሱት ከፍተኛ መኮንኖች አንዱ የሆኑት ተወልደ ገ/ትንሳኤ (ዕምበብ) በቅርቡ ከአገር መውጣታቸው ሚንስትር አቶ ጌታቸው ረዳ በቅርቡ ከፋና ቴሌቪዥን በነበራቸው ቆይታ ጠቅሰዋል።

አቶ ጌታቸው አስቀድመ ይዘውት እንደወጡ የገለጹትን ሰነድ ይህ ብቻ ሳይሆን በርካታ የተሸሸጉ ወንጀሎችን የሚያጋልጡ መረጃዎችንም እንደሚያካትት እየተገለጸ ነው። ከአዲሱ ፓርቲያቸው ምስረታ ጋር ተያይዞ አያወጡ ያለው መረጃ ሊጎዳቸው እንደሚችል ርዕዮት ሚዲያ ጠቁሟል። መረጃው ሃሰት ይሆናል በሚል ሳይሆን በመንግስት ሚዲያ መናገራቸው ዋጋ እንደሚያስከፍላቸው ገልጿል። ይልቁኑ በርዕዮት በኩል ወይም ዪኤም ኤስ ብኩል መናገር እንደነበረባቸው አመልክቷል።

ለምን በመንግስት ሚዲያ ተናገሩ በሚል አንዳንድ ቅሬታ ቢሰማ፣ አቶ ጌታቸው ዙሩን እንደሚያከሩት ነው እየተሰማ ያለው።

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
የኢትዮጵያ ነርሶች ማህበር ታካሚዎች ለሞትና እንግልት እንዳይዳረጉ አስጠነቀቀ
የውጭ ባንኮች 2018 አጋማሽ ላይ ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2