Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ታላቁ ህዳሴ ግድብ በመገባደጃ ምዕራፍ ላይ

    April 1, 2023

    የአሊባባ ግሩፕ በኢትዮጵያ የኢኮሜርስ ገበያ ለመጀመር የሚያስችል ስራ መጀመሩን ይፋ አደረገ

    August 22, 2024

    ዶናልድ ትራምፕ በቁጥጥር ሥር ውለው በቀረበባቸው ሰላሳ አራት ክሶች ጥፋተኛ አይደለሁም አሉ

    April 6, 2023

    የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ሰነድ የሌላቸው የኤርትራዊ ስደተኞች መታሰራቸውን ኮነን፤ “ያለ ህጋዊ ማስረጃ የትኛው አገር መኖር ይቻላል?”

    June 4, 2023

    ቻይናዊው የፀሃይ ሪል ስቴት ዋና ስራ አስኪያጅ ከ9 ግብረ አበሮቻቸው ጋር የውጭ አገር ብሮች በማተምና በጥቁር ገበያ ወንጀል ታስረው ፍ/ቤት ቀረቡ

    September 5, 2023
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  News  ብርቱካንን ጨምሮ 16 ግለሰቦች በኢ.ቢ.ኤስ ቴሌቪዥን የሀሰተኛ መረጃ ስርጭት፣ የሽብር ወንጀልን ጨምሮ በሶስት ክሶች ተከሰሱ
News

ብርቱካንን ጨምሮ 16 ግለሰቦች በኢ.ቢ.ኤስ ቴሌቪዥን የሀሰተኛ መረጃ ስርጭት፣ የሽብር ወንጀልን ጨምሮ በሶስት ክሶች ተከሰሱ

Ethioreview newsEthioreview news—May 7, 2025
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ተከሳሾቹ ዛሬ ከሰዓት በኋላ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የፀረ ሽብር ወንጀል ችሎት ቀርበው በተፈጸመው የወንጀል ድርጊት እንደየተሳትፏቸው የቀረበባቸው ክስ ተነቦላቸዋል፡፡

ጠቅላይ አቃቤ ህግ ዛሬ ክስ የመሰረተባቸው ግለሰቦች በአሜሪካና በሃገር ውስጥ የሚገኙ ሲሆን፥ መዓዛ መሐመድ፤ ተስፋዬ ወልደሰላሴ፣ ኢ.ቢ.ኤስ ቴሌቭዥን ኃ.የተ.የግ/ማህበር፣ በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ተቋማት የሚሰሩ አመራሮችና ብርቱካን ተመስገንን ጨምሮ 16 ግለሰቦች ናቸው።

ከ1ኛ እስከ 6ኛ ያሉ ተከሳሾች በ1996 ዓ.ም በወጣው የወንጀል ህግ አንቀጽ 32 (1) (ሀ) (ለ) እና የሽብር ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በወጣው አዋጅ ቁጥር 1176/2012 አንቀጽ 3/1/ለ/ ስር የተደነገገውን በመተላለፍ ክስ ቀርቦባቸዋል።

ተከሳሾች ለጊዜው በቁጥጥር ስር ካልዋሉ ሌሎች ግብራበሮቻቸው ጋር በመሆን የፖለቲካ ዓላማን በኃይል ለማስፈፀም በማሰብ በህገ መንግስት የተቋቋመውን የፌደራልና የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስትን በኃይል በማስወገድ ስልጣን ለመያዝ፤ ይህ ካልተሳካ ደግሞ መንግስትን በሀይል በማስገደድ ለድርድር እንዲቀመጥ ማድረግ የሚል ዓላማን በመያዝ መንቀሳቀሳቸው በክሱ ተመላክቷል።

More stories

“ትህነግ ከጁንታነትም ወርዶ በየጫካው ተሹለክላኪ የእህል ሌባ ሆኗል፣ ከያለበት እየታደነ ነው “ሜ/ጀ መሐመድ ተሰማ

April 7, 2021

የመ/ሰራዊትን መለያ ለብሶ ከሱዳን ወደ ወልቃይት ሊገባ የነበረ የትህነግ የሽብር ሃይል ተደመሰሰ፤ አንገታቸው የተቀላ መኮንኖች ፊልም ሊታዩ ነው

May 13, 2021

ከሱዳን የተነሳ የትህነግ ሃይል (ሳምሪ) ሳይዋጋ ሙሉ በሙሉ ተማረከ

August 11, 2021

የመንግስት ማጅራት መቺዎች ፈተና ሆነዋል – ሃላፊዋ አምነዋል

May 9, 2022

ተከሳሾቹ ይህንን ዓላማቸውን ለማሳካት በአማራ ክልል በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች የሚማሩ የኦሮሞ ብሔር ተወላጅ ተማሪዎች ላይ ከፍተኛ ጥቃት እንዲደርስባቸዉ በማድረግ በአፀፋዉ በኦሮሚያ ክልል የሚኖሩ የአማራ ብሄር ተወላጆች ላይ የኦሮሞ ብሄር ተወላጆች አደጋ እንዲያደርሱ በማድረግ የህዝቡን ሕይወትና ንብረት ለከፍተኛ አደጋ በማጋለጥ በሀገሪቷ ውስጥ ከፍተኛ ትርምስ ለመፍጠር ማሴራቸውም ተብራርቷል።

በዚህም ኢትዮጵያ ውስጥ የሕግ በላይነት እንዳይኖርና መጨረሻ የሌለው ከፍተኛ የሰው ሕይወት እልቂት እንዲከሰት በማድረግ መንግስት ሀገሪቷን ተረጋግቶ እንዳያስተዳድር፣ የሀገሪቷን አንድነትና ሉዓላዊነት እንዳያስጠብቅ፣ የዜጎችን በሰላም የመኖር መብትን እንዳያስከብር፣ ለሰዉ ሕይወትና ንብረት ደህንነት ዋስትና እንዳይሆን በማድረግ አጋጣሚውን በመጠቀም ተከሳሾቹ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ሆነዉ በመናበብ የተመደቡበትን የስራ ኃላፊነትን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ከመስከረም ወር 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ መጋቢት ወር 2017 ዓ.ም ድረስ መንቀሳቀሳቸውን ክሱ ያሳያል።

የተለያዩ ሀሰተኛ መረጃዎችን በማዘጋጀትና ለ6ኛ ተከሳሽ ብርቱካን ተመስገን ያስጠኑትን ሀሰተኛ ታሪክ እውነተኛ ታሪክ አስመስሎ በመቅረጽና በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ላሉ ዜጎች እንዲደርስ በማድረግ በሕዝቡ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣ እንዲቀሰቀስ ማድረጋቸው ነው አቃቤ ህግ በክሱ ያስረዳው።

በዋናነትም 6ኛ ተከሳሽ በደምቢዶሎ ዩኒቨርስቲ ተማሪ በነበረችበት ወቅት ተጠልፋ እንደተደፈረች በማሰመሰል፤ ሀሰተኛ መታወቂያን ጨምሮ የገንዘብ ድጋፍና እቅድ አውጥቶ በመስጠትና በመተግባር በመሳተፋቸው ተከሳሾቹ የሽብር ወንጀል ክስ ቀርቦባቸዋል።

ሁለተኛው ክስ ከ7ኛ እስከ 11ኛ ተከሳሾች ባሉ ተከሳሾች ላይ የቀረበ ሲሆን፥ በ1996 ዓ.ም በወጣው የወንጀል ህግ አንቀጽ 32 (1) (ሀ) እና (ለ)፣ 34፣ 43 (3)፣ 46 እና የጥላቻ ንግግርና የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በወጣው አዋጅ ቁጥር 1185/2012 አንቀጽ 4፣ 5 እና 7/4 ስር የተደነገገውን በመተላለፍ ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡

7ኛ ተከሳሽ ኢ.ቢ.ኤስ ቴሌቭዥን ኃ.የተ.የግ/ማህበር እና 8ኛ ተከሳሽ ሲልቨር ስፕሪንግ ፕሮዳክሽንና ፕሮሞሽን ኃ.የተ.የግ.ማህበር (የኢ.ቢ.ኤስ ቴሌቭዥን የእህት ኩባንያ) ሆኖ የ6ኛ ተከሳሽ ታሪክ የተላለፈበትን ፕሮግራም የሚመራ፣ 9ኛ ተከሳሽ ማክዳ ፍስሓጽዮን /ማክዳ አሰፋ/ የሲልቨር ስፕሪንግ ፕሮዳክሽንና ፕሮሞሽን ስራ አስኪያጅና የኢ.ቢ.ኤስ የመዝናኛ ፕሮግራሞች ሃላፊ፣ 10ኛ ተከሳሽ ታሪኩ ሀይሌ ረታ በኢ.ቢ.ኤስ ቴሌቭዥን የአዲስ ምዕራፍ ፕሮግራም ዳይሬክተር፣ 11ኛ ተከሳሽ ህሊና ታረቀኝ አረጋ በኢ.ቢኤስ ቴሌቭዥን የአዲስ ምዕራፍ ፕሮግራም ረዳት ናቸው፡፡

በተለይም 9ኛ ተከሳሽ የ6ኛ ተከሳሽ ብርቱካን ተመስገን ታሪክ እውነተኝቱና ትክክለኛነቱ የሚያጠራጥር ነው፤ የዩኒቨርስቲው ስም ባይጠቀስም ባለፉት ዓመታት የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ታገትው ጠፉ ከተባሉት ጋር የሚገናኝ ታሪክ ስለሚመስል አሁን የተቀረፀው ፕሮግራም ከተሰራጨ በኋላ ሰዎች የሚረዱት የጠፉት ተማሪዎች እጣ ፋንታ ሞተዋል ማለት ነው የሚል ድምዳሜ ላይ የሚያስደርስ ሊሆን ስለሚችልና ይህ ታሪክ ከተሰራጨ ሁከትና ብጥብጥን አስነስተዉ የሰውን ሕይወት ለአደጋ የሚያጋልጥ በመሆኑና ታሪኳ ልክ ባለመሆኑ ኢክስኪውቲቭ ፕሮዲውሰር ዉሳኔ እንዲሰጡበት እንጠይቃለን የሚል አስተያየት የ7ኛ ተከሳሽ (ኢ.ቢ.ኤስ ቴሌቭዥን ኃ.የተ.የግ/ማህበር) የሕግ ክፍል ቢያቀርብላትም አስተያየቱንና የስራ ኃላፊነቷን ወደ ጎን በመተው ትክክለኛ ያልሆነ የተቀነባበረ ታሪክ በቀን 14/7/2017 ዓ.ም በኢ.ቢ.ኤስ ቴሌቭዥን አዲስ ምዕራፍ ፕሮግራም ለብዙ ሕዝብ እንዲደርስ ያደረገች በመሆኑ ክሱ ተመስርቶባታል።

10ኛ ተከሳሽ ታሪኩ ሀይሌ ረታ የአዲስ ምዕራፍ ፕሮግራም ዳይሬክተርና 11ኛ ተከሳሽ ህሊና ታረቀኝ ረዳት ዳይሬክተርነት የ6ኛ ተከሳሽ ብርቱካን ተመስገን በአካል ያገኟት በመሆኑ ታሪክ ውስጥ ብዙ የሚያጠራጥሩ እውነት የማይመስሉ ንግግሮች እያሉ፣ በበቂ ማስረጃ ማረጋገጥ እየቻሉ ባለማድረግ ግብረአበር በመሆን በፈፀሙት የጥላቻ ንግግርና ሀሰተኛ መረጃ ስርጭት ወንጀል ተከስሰዋል፡፡

3ኛው ክስ በ3ኛ፣ በ6ኛ እና ከ12ኛ እስከ 16ኛ ባሉት ተከሳሾች ላይ የቀረበ ሲሆን፤ ተከሳሾቹ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀጽ 32(1) (ሀ) እና (ለ)፣ 33 እና የሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 9(2) በመተላለፍ ነው ክስ የተመሰረተባቸው።

ተከሳሾች በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በመላ ሃሳባቸው፣ በወንጀሉ ድርጊትና በሚሰጠው ውጤት ሙሉ ተካፋይ በመሆን የማይገባ ጥቅም ለ6ኛ ተከሳሽ ብርቱካን ተመስገን ለማስገኘት አስበዉ የተሰጣቸዉን ስልጣንና ኃላፊነት በግድፈት ያለአግባብ በመገልገል ሀሰተኛ የነዋሪ መታወቂያ እንዲሰጣት በማድረግ፤ እውነተኝነቱ ሳይረጋገጥ በአስገድዶ መደፈር ምክንያት ለልብ ሕመም በሽታ እንደተዳረገች፣ የኢኮኖሚ አቅምና ቤተሰብ እንደሌላትና እገዛ እንደምትፈልግ እንድትገልጽ ድጋፍ በማድረግ የማይገባትን ሶስት ሚሊዮን አንድ መቶ ዘጠኝ ሺ ስምንት መቶ ሰማኒያ ሁለት ብር በመጋቢት ወር አጋማሽ 2017 ዓ.ም ከተለያዩ ግለሰቦች ወደ የባንክ ሂሳብ ቁጥሯ እንዲገባላት ሁኔታ ያመቻቹ መሆናቸው በክሱ ተዘርዝሯል።

በዚህም ተከሳኞቹ በፈፀሙት በስልጣን አለአግባብ መገልገል ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸዋል፡፡

ከዚሁ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የነበሩ አራት ግለሰቦች በዋስትና እንዲለቀቁ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የፀረ ሽብር ወንጀል ችሎት የግራነና ቀኙን ክርክር ለመስማት ለግንቦት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

በሲፈን መኮንን


ኢትዮሪቬውን ከታች ባሉት ማስፈንጠሪያዎች የከተሉ – የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ ፡  @ethioreview
ፌስቡክ ገጻችንን ላይክ ያድርጉ ፡ ethioreview
ኤክስ ፡ twitter


NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ከኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር በድምፃዊ አስጌ ላይ የተሰጠ መግለጫ
“ጀነራሉ ያዋቀሩት ካቤኔ እና እየሄዱት ያለው አካሄድ የነበረውን ሰላም የሚያሳጣ ነው ” የኢሮብ ሲቪክ ማህበር
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE - VOICES OF ETHIOPIA
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2