ኢራን አሜሪካን ላይ የአጸፋ እርምጃ ከሞከረች ስህተቱ ከቀደመው ሁሉ የከፋ ስህተት ይሆናል ተባለ፤ ምላሹ የከፋ ነው ብትልም ዛቻው አልቆመመ። የኢራን የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር የአሜሪካ ጥቃት “የማያባራ መዘዝ” ያስከተላል” ነው ያሉት። ይሆናል አይሆንም የሚታይ ቢሆንም እስራኤልን ግን እየተመታች ነው። እሷም የተመረጡ ስትራቴጂክ ስፍራዎችን እያወደመች ነው።
ይህ አሰላለፍን እያጸዳ ያለው ጦርነት አገራት አቋማቸውን ይፋ ማድረጋቸውን ተከትሎ ይፋ እየሆነ ነው። ዩናይትድ ኪንግደም ከአሜሪካ ጎን መቆሟን በግልጽ አሳይታለች፡፡ ለኢራን ከፍተኛ ማስጠንቀቂያ አስተላለፈች። የዩናይትድ ኪንግዶም አንድ ከፍተኛ ባለሥልጣን፣ “ኢራን በአሜሪካ ወታደሮች ላይ ጥቃት ከፈጸመች፣ ጥቃቱ በኔቶ (NATO) ሀገራት ላይ እንደተፈጸመ ጥቃት እንቆጥረዋለን” ብለዋል። ጀርመንና ፈረንሳይም ተመሳሳይ አቋም አላቸው።
የዩናይትድ ኪንግዶም ባለስልጣን ንግግር ኢራን በአሜሪካ ላይ የምትወስደው ማንኛውም እርምጃ መላውን የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) ወደ ግጭቱ ሊያስገባ እንደሚችል የሚያስጠነቅቅ ሲሆን፣ የውጥረቱን መጠን ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ መሆኑ ተዘግቧል።
ይህ የተባለው አሜሪካ የኢራንን የኒውክሌር ማብላያዎችን የመጨረሻ ባለችው ቴክሎጂና ቦምቦች ተጠቅማ የተሳካ ያለችውን ጥቃት መፈፀሟን ማስታወቋን ተከትሎ ኢራን የበቀል እርምጃ እንደምትወስድ በማስታወቋ ነው።
አሜሪካ እጅግ ውጤታማ ያለችውን ድብደባ የኢራን አልካደችም። ነገር ግን ይህ ነው ሚባል ጉዳት እንዳልደረሰና ጥቃቱ ያረፈው የኒውክሌር ማብላያ ተቋሞቹ ህንፃዎች ላይ እንጂ አብዛኛውን የኒውክሌር ማብላያ ግብዓትና መሳሪያዎች ራቅ ወዳሉ አከባቢዎቸ ከተዘዋውሩ መሰነባበቱን የሚጠቁም መረጃ ተሰምቷል። ይህ መረጃ ግን ብዙም የሚታመን አልሆነም። እንደውም የልጆች ቀልድ ዓይነት እንደሆነ የሚገልጹም አሉ። እንደዚህ የሚሉት አካላት የሚያስጨንቃቸው ኢራን በዕልህ ልቅ ወደ ሆነ ጥቃት እንዳታመራ ነው። ይህ ከሆነ ደግሞ አሜሪካ ውሳኔዋ ይከፋል።
ጥቃቱ ምን ይመስል ነበር?
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ ብሔራዊ የቴሌቪዥን ንግግር ሲያደርጉ ዓለም ትንፋሹን ውጦ ያዳምጥ ነበር። ቃላቶቻቸው እንደተወነጨፈ ጥይት ቀጥተኞች ነበሩ። “ዛሬ ማታ፣ ለአሜሪካ ህዝብ እና ለመላው ዓለም አስታውቃለሁ” አሉ ፕሬዝዳንቱ በልበ ሙሉነት። “የአሜሪካ ጦር በኢራን በሚገኙ ሦስት የኑክሌር ተቋማት ላይ እጅግ በጣም የተሳካ ጥቃት ፈጽሟል። ፎርዶው፣ ናታንዝ እና ኢስፋሃን ሙሉ በሙሉ ወድመዋል። ፎርዶው ከጥቅም ውጪ ሆኗል!”
ይህ መግለጫ፣ ለዓመታት ሲጠበቅ የነበረው ነገር ግን ማንም እንዲሆን ያልደፈረው ቀይ መስመር መሻገሩን የሚያበስር ነበር። የአሜሪካ B-2 ስውር ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች፣ በተራራ ውስጥ በጥልቀት የተገነባውን የፎርዶው የኑክሌር ማበልጸጊያ ምሽግ ለመስበር ተብለው የተሰሩትን “ባንከር በስተር” የተባሉ ከባድ ቦምቦችን አዝንበውበታል።
የፕሬዝዳንቱን ንግግር ተከትሎ ይፋ የሆኑ የሳተላይት ምስሎች፣ የጥቃቱን አስፈሪነትና የኢራንን ቅድመ ዝግጅት አስመልክቷል። ጥቃቱ ከመፈጸሙ ከቀናት በፊት፣ በፎርዶው መግቢያ ዋሻዎች ላይ ከፍተኛ እንቅስቃሴ ነበር። የጭነት መኪኖችና ከባድ ማሽነሪዎች፣ የአየር ጥቃትን ለመቋቋም በማሰብ ይመስላል፣ ዋሻዎቹን በአፈር ሲሞሉ ታይተዋል።
ነገር ግን ከጥቃቱ በኋላ የተነሱት ምስሎች፣ የኢራን ጥረት እንዳልተሳካ አሳይተዋል። ተራራው ራሱ የቆሰለ ይመስላል፤ መሬቱ ወደ ውስጥ ተደርምሷል፤ ምሽጉ ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን የሚያሳዩ ምልክቶች በግልጽ ይታያሉ። የቴክኖሎጂ ጦርነት በሰማይ ላይ ሳይሆን፣ በመሬት ውስጥ በሚስጥር በተገነባው የኢራን የኑክሌር ህልም ላይ የተፈጸመ ይመስላል።
የኢራን ምላሽ ምን ሆነ?
የሌሊቱ ጸጥታ በድንገት በሚያስገመግሙ የፍንዳታ ድምጾች እና በከተማዋ ላይ በሚያስተጋቡ የአደጋ ጊዜ ሳይረኖች ተሰማረ። ከኢራን የተተኮሱ ከ20 በላይ ኃይለኛ ሚሳኤሎች የእስራኤልን ሰማይ ሰንጥቀው በቴል አቪቭ እና ሃይፋ ከተሞች ላይ ሲያርፉ፣ ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ የፍርሃትና የትርምስ ማዕበል ተቀሰቀሰ። የመኖሪያ ህንጻዎች ወደ ፍርስራሽነት ተቀየሩ፤ የቆሙ መኪኖች ተጨማደዱ፤ የተጎዱ ሰዎችን ለማውጣት የነፍስ አድን ሰራተኞች በተሰባበሩ ኮንክሪቶችና ብረቶች መካከል ሲሯሯጡ ይታያል። ጦርነቱ ከስውር ጥላ ወደ ግልጽ እውነታ የተቀየረበት ምሽት ነበር።
ይህ አስደንጋጭ የበቀል እርምጃ፣ ከመላው ዓለም ሰዓታት በፊት የተነገረውን አንድ ዜና ተከትሎ የመጣ ነበር።ከጥቂት ሰዓታት በፊት፣
የኢራን ምላሽ ፈጣንና ግልጽ ነበር። በእስራኤል ከተሞች ላይ የሚሳኤል ውርጅብኝ እየዘነበ ባለበት ወቅት፣ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በቱርክ ለተሰበሰቡ ጋዜጠኞች መግለጫ ሰጡ። ፊታቸው በቁጣ ተሞልቶ ነበር። “የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ አባል የሆነችው ዩናይትድ ስቴትስ፣ ሰላማዊ የኑክሌር ተቋሞቻችንን በመደብደብ የተመድን ቻርተር፣ ዓለም አቀፍ ህግን እና የኑክሌር ስምምነትን ክፉኛ ጥሳለች” ሲሉ ከሰሱ።
ቃላቶቻቸው ከክስነት ወደ ማስጠንቀቂያ ተሸጋገሩ። “በተመድ ቻርተር መሰረት ራሳችንን የመከላከል ህጋዊ መብታችንን ተጠቅመን፣ የሀገራችንን ሉዓላዊነት፣ ጥቅም እና ህዝብ ለመጠበቅ ማንኛውንም አማራጭ እንወስዳለን።” ሲሉ ነበር ሚኒስትሩ ንግግራቸውን የደመደሙት፣ “በበላይ መሪያችን ላይ የሚቃጣ ማንኛውም እርምጃ ሁሉንም ቀይ መስመሮች መሻገር ነው፤ ምላሻችንም ገደብ የለሽ ይሆናል” በሚል አስፈሪ ዛቻ ነበር።
ይህን ቢሉም አሁን እየወጡ ያሉት መረጃዎች የኢራን መሪ ከስልጣን ሊነሱ እንደሚችሉ ነው። በሌላም በኩል ለማንኛውም በሚል ራሳቸው ተጠባባቂ እሳቸውን የሚተኩ መሪዎች መሰየማቸው ተሰምቷል።
ዛቻው አለቀረም። እስራኤል ከኢራን በተተኮሱ ሚሳይሎች ህንጻዎቿ እየፈረሱ ነው። ውድመቱ ከቀድሞዎቹ የባሰና ከፍተኛ ጉዳይ ያደረሱ መሆናቸው ከሚወጡ የቪዲዮና የምስል መረጃዎች ማረጋገጥ ተችሏል።
እስራኤልም በበኩሏ በተመረጡ ስፋራዎች ላይ ጥቃት እየፈጸመች ሲሆን ስድስት የአየር ማረፊያዎችንና አስራ አምስት አውሮፕላኖች ማውደሟን አስታውቃለች። ክድብደባው ጀርባ የሹም ሽር ወሬም እየወጣ ነው።
ለክፉውም መዘጋጀት ይበጃል ያሉት የኢራኑ መሪ አያቶላህ አሊ ኻምኒ ሶስት ተተኪዎችን መርጡ።
ጦርነቱ ተባብሶ በቀጠለበት እና በቀጣይም በጦርነት ውስጥ የሚሆነው ለማይታወቅበት ኢራን ከእስራኤል እያደረገች ባለው ፍልሚያ እና አሜሪካ ወደ ጦርነቱ ለመግባት ጫፍ ላይ ባለችበት ቅፅበት የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻምኒ ለክፉው ራሳቸውን አዘጋጅተዋል ተብሏል።
ኒውዮርክ ታይምስ የኢራንን ባለስልጣናትን ጠቅሶ እንደዘገበው፤ ኻሚኒ እሳቸው ሲሞቱ በእጩነት ለመሾም ሶስት ከፍተኛ የሀይማኖት አባቶችን ቢያቀርቡም ማንነታቸው አልተገለጸም ሲል ሚድል ኢስት የአረበኛው ክፍል ዘግቧል።
ከእስራኤል ጋር እየተካሄደ ባለው ጦርነት ፈጣን እና ሥርዓት ያለው የስልጣን ሽግግር ማረጋገጥ ይፈልጋሉም ተብሏል። የኢራን የስለላ ድርጅት ከፍተኛ ባለስልጣናት የሞባይል ስልኮችን ወይም ማንኛውንም የኤሌክትሮኒክስ የመገናኛ ዘዴዎችን መጠቀም እንዲያቆሙ እና ከመሬት በታች ባሉ ጋሻዎች ውስጥ እንዲቆዩ መጠየቁን ገልጿል ሲል ሚድል ኢስት ዘግቧል።
በደቡባዊ እስራኤል በከባድ ሚሳኤሎች ዋና ዋና የእስራኤል የስለላ ተቋማት፣ የሞሳድ መስሪያ ቤት፣ ለወታደራዊ ጥቅም የሚውሉ የቴክኖሎጂ ማእከሎች እና በቴል አቪቭ፣ በሀይፋና ቤርሸባ ያሉ ከተሞች ከተመቱ በኋላ አያቶላህ አሊ ኻሚኔ በስልጣን ላይ እንዲቆዩ “ሊፈቀድለት አይችልም” ስትል እስራኤል ሐሙስ ተናግራ ነበር ብሏል ዘገባው።
እስራኤል እንደ ኢራን ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ያሉ የኒውክሌር ወይም የባላስቲክ ሚሳኤል ስፍራዎች ላይ ኢላማ መደረጉን ተከትሎ የእስራኤል ትክክለኛ አላማ የኢራንን የኒውክሌር እና የባሊስቲክ አቅም ከማዳከም ባለፈ የጠቅላዩ መሪ አሊ ኻሚኒን ከስልጣን መውረድን ትፈልጋለች ተብሏል።
የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ
ሌላው አዲሱ ትኩሳት የኢራን ፓርላማ የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ እንዲዘጋ የቀረበውን ውሳኔ ማጽደቁ ነው። ይህ ርምጃ በኣለም የነዳጅ ስርጭት ላይ ከፈተኛ ጫና ስላለው ቻይና እንድታረግበው ተጠይቃለች።
የሆርሙዝ ወንዝ የዓለም ኢነርጂ የደም ቧንቧ የሚባልለት ሲሆን፤ በግምት 20 – 30 በመቶ የሚሆነው የዓለማችን የነዳጅ ዘይት በሆርሙዝ ሰርጥ ላይ ያልፋል። የዚህ ሰርጥ መዘጋት ዓለም አቀፍ የኢነርጂ ደህንነት ላይ ስጋትን የሚደቅን ተደርጎ ይወሰዳል። ሰርጡ ከተዘጋ የነዳጅ ዘይት ዋጋ ከፍተኛ ጭማሪ እና የአቅርቦት መቆራረጥ ያስከትላል ተብሏል።


