Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  POLITICS  ኢዜማ እስር ላይ ያሉት መሪው ዶክተር ጫኔ የድርጅቱን መርህ መጣሳቸውን በይፋ አስታወቀ
POLITICS

ኢዜማ እስር ላይ ያሉት መሪው ዶክተር ጫኔ የድርጅቱን መርህ መጣሳቸውን በይፋ አስታወቀ

Ethioreview newsEthioreview news—October 2, 2023
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ኢዜማ እስር ላይ ያሉት የድርጅቱ መሪ ዶክተር ጫኔ ከበደ የድርጅቱን መርህ መጣሳቸውን በይፋ አስታወቀ። ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ ከድርጅቱ መርህ ውጭ ባፈነገጠ መልኩ መንቀሳቀስ ኢዜማን እንደማፍረስ እንደሚቆጠር አስታውቋል። የድርጅቱን መርህና አሰራር የዘርዘረው መግለጫ ” የፓርቲያችን ሊቀመንበር ጉዳይም ከዚህ ከላይ ከተገለፀው መርኅ አንጻር የሚታይ ይሆናል ሲል ፓርቲያችን ይገልፃል” ሲል አቋሙን ይፋ አድርጓል። <<…ከሰላማዊ ትግል እና ከዜግነት ፖለቲካ እንቅስቃሴዎች ውጭ ያለን የፖለቲካ እንቅስቃሴ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ መደገፍ፣ የሀሳብም ሆነ የተግባር ተሳትፎም ሆነ ትብብር ማድረግ ከኢዜማዊነት መርኅ ማፈንገጥ መሆኑን ለማስገንዘብ እንወዳለን::>> ብሏል

ኢዜማ ከሰላማዊ የትግል ስልት ውጪ በዘውጌ ብሔርተኝነትም ሆነ አፈሙዝ በታከለበት የትግል መንገድ መንቀሳቀስን ድርጅቱ የቆመበትን መርኅ መቃረን አድርጎ ያየዋል። ማንኛውም የኢዜማ አባል ብሎም ከወረዳ እስከ ብሔራዊ ስራ አስፈፃሚ ድረስ የሚሳተፍ አመራር ከዚህ የድርጅቱ ፅኑ ዕምነት ውጭ የተንቀሳቀሰ እንደሆነ ድርጅቱን ለማፍረስ እንደሚሰራ ተደርጎ እንደሚቆጠር መታወቅ አለበት። ኢዜማ ውስጥ የማይነካም ሆነ የማይተካ አባልም ሆነ አመራር የለም! ስለሆነም ከድርጅቱ ዓላማ እና የትግል መስመር ባፈነገጠ መንገድ በሚንቀሳቀሱ አባላቱ ላይ የፀና አቋም ይይዛል።

ኢዜማ የሊቀመንበሩን መታሰር በተመለከተ የሰጠው መግለጫ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) መስከረም 14 ቀን 2016 ዓ.ም የፓርቲያችን ሊቀመንበር ዶ/ር ጫኔ ከበደ በጸጥታ አካላት በቁጥጥር ሥር መዋልን አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ ጉዳዩን በጥንቃቄና በትኩረት እንደሚከታተለው፣ መረጃዎችንም በተከታታይ እንደሚያሳውቅ መግለፁ የሚታወስ ነው፡፡

በዚሁ መሠረት የፓርቲያችን ብሔራዊ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይህንኑ ጉዳይ እንዲከታተል የሰየመው ኮሚቴ ባደረገው ማጣራት ዶ/ር ጫኔ ከበደ በቁጥጥር ስር የዋሉት በፓርቲያችን ባላቸው ኃላፊነት ሳይሆን በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መሠረት በኮማንድ ፖስቱ ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የዋሉ መሆኑን መረጃዎች አግኝተናል፡፡

More stories

ደቡብ ሱዳን ስድስተኛ ሀገር ሆና የናይል ስምምነት ማዕቀፍን አጸደቀች

July 12, 2024

“ትህነግ ጦሩን እስጠግቷል፤ የጦርነት ስጋት አለብን” የጠለምት ወሰንና ማንነት አስመላሽ

June 7, 2025

“የኢትዮጵያን ህልውና የሚበይኑት የተፈጥሮ ሀብቶች…”

September 2, 2024

“ዘመን ትውልድን ይገነባል ፤ ትውልድም ዘመንን ይገነባል”

September 10, 2023

ይህ መረጃ ከተገኘ በኋላ የብሔራዊ ሥራ አስፈፃሚው ኮሚቴ መስከረም 19 ቀን 2016 ዓ.ም ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ በጉዳዩ ላይ በጥልቀት ተወያይቷል።

በአሁኑ ወቅት ሃገራችንን ሰቅዞ የያዘው የፖለቲካ ውጥረት መነሻ በሁለት እሳቤዎች መካከል በሚደረግ ፅንፍ የረገጠ መካረር መሆኑ እሙን ነው ፡፡ በአንድ በኩል በእውቀት፣ እውነት፣ መርኅ እና ምክንያታዊነት ምሶሶዎች ላይ የተመሠረተው የዜግነት ፓለቲካ፤ ከዚህ በተለየ ደግሞ ተበደልኩ፣ ተገለልኩ፣ የሚገባኝን ያህል የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት እና የፖለቲካ ውክልና ተነፍጎኛል . . . ባህሌን፣ ቋንቋዬን እና ወግ ሥርዓቴን ማሳደግ አልቻልኩም በሚሉ በዘውግ ላይ በተንጠለጠለ ልዩነትን መሰረት ባደረገ የማንነት ፖለቲካ መካከል ሲደረግ የቆየው ግብግብ ከፍተኛ ደረጃ ላይ በመድረሱ ነው ብለን እናምናለን።

በሁለቱ የፖለቲካ መስመሮች መካከል የሚደረገው ትንቅንቅ የሚያስከትለውን የሕይወት እና የንብረት ውድመት፣ በአጠቃላይ ህዝባችንን ከችጋር እና ጉስቁልና በሚያላቅቅ የልማት ሥራ ላይ መዋል ያለበት ውስን የሀገር ኃብት ብክነትን በማስቀረት ከትጥቅ ትግል ይልቅ በመተማመን ላይ የተመሠረተ የሃሳብ ትግል (በሰላማዊ ንግግር ችግሮችን መፍታትን ልንከተለው የሚገባ ብቸኛ የትግል ስልት) እንደሆነ የሚያሳይ አቋማችንን ደግመን ደጋግመን የገለፅነው የአደባባይ ሃቅ ነው።

ኢዜማ በመርኅም ሆነ በተግባር በዜግነት የፖለቲካ አስተሳሰብ እና በፀና የሰላማዊ ትግል መስመር የሚያምን፣ ይህንኑ መርኅ ብቻ ተከትሎ የሚሠራ፣ በማንኛውም ዓይነት ሁኔታ በዘውግ ተኮር የፖለቲካ እንቅስቃሴም ሆነ በኃይል መንግሥታዊ ሥልጣን ለመያዝ በሚደረግ ትግል ውስጥ ፈጽሞ የማይሳተፍ ብቻ ሳይሆን በዚህ መንገድ ተጉዘን ዕረፍት ለናፈቀው ህዝባችን የሰላም አየር ልናመጣለትም ሆነ በዘላቂነት ወደተረጋጋ የፓለቲካ ሥርዓት ልንደርስ እንደማንችል ያለጥርጥር የሚያምን ድርጅት ነው፡፡

ኢዜማ ከሰላማዊ የትግል ስልት ውጪ በዘውጌ ብሔርተኝነትም ሆነ አፈሙዝ በታከለበት የትግል መንገድ መንቀሳቀስን ድርጅቱ የቆመበትን መርኅ መቃረን አድርጎ ያየዋል። ማንኛውም የኢዜማ አባል ብሎም ከወረዳ እስከ ብሔራዊ ስራ አስፈፃሚ ድረስ የሚሳተፍ አመራር ከዚህ የድርጅቱ ፅኑ ዕምነት ውጭ የተንቀሳቀሰ እንደሆነ ድርጅቱን ለማፍረስ እንደሚሰራ ተደርጎ እንደሚቆጠር መታወቅ አለበት። ኢዜማ ውስጥ የማይነካም ሆነ የማይተካ አባልም ሆነ አመራር የለም! ስለሆነም ከድርጅቱ ዓላማ እና የትግል መስመር ባፈነገጠ መንገድ በሚንቀሳቀሱ አባላቱ ላይ የፀና አቋም ይይዛል።

ኢዜማዊነት በምንም መንገድ ሁለት የማይታረቁ ሃሳቦችን እያጣቀሱ መሄድን የማይፈቀድ እንደሆነ መላው የድርጅታችን አባላት፤ እንደዚሁም በክብር፣ በነፃነት እና በእኩልነት የመኖር ዋስትና እንዲረጋገጥለት ዘወትር የምንታገልለት መላው የኢትዮጰያ ህዝብ እንዲያውቅልን እንፈልጋለን።

ሀገራችን ከገባችበት የፖለቲካ ምስቅልቅል ደረጃ በደረጃ ልትላቀቅ የምትችለው በፖለቲካ ምኅዳሩ ላይ የምንሳተፍ ኃይሎች (መንግሥት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ሲቪል ማኅበራት፣ የመገናኛ ብዙኋን፣ . . . እና መላው የሃገራችን ዜጎች) ሕጋዊ እና ሰላማዊ የሆነ ትግልን በመከተል እና ከዛ ውጪ ያለ አማራጭ የትግል መስመር ውስጥ ባለመሳተፍ እና ባለመደገፍ እንደሆነ እናምናለን። በተለይ በአሁኑ ሰዓት የሃገራችንን መሠረታዊ ችግሮችን ሥርዓት ለማስያዝ እንደሃገር ብዙ ተስፋ የሰነቅንበት ሃገራዊ ምክክር ሊጀምር በመሆኑ ትኩረታችን እሱ ላይ መሆን አለበት ብለን በጽኑ እናምናለን።

የሃገራዊ ምክክሩን ውጥኖች ተግባራዊነት በማረጋገጥ ነፃ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥታዊ ሥልጣን የሚያዝበት ብቸኛው መንገድ እንዲሆን፣ እና ከዛ ውጪ ያሉት አማራጮች በኢትዮጵያ ምድር የማይሞከሩ ብቻ ሳይሆኑ የማይታሰቡም ጭምር እንዲሆኑ ማድረግ ያስፈልጋል ብለን እናምናለን።

በሃገር ውስጥም ሆነ ከሃገር ውጪ የሚገኙ አባላት እና ደጋፊዎች ከመርኀችን እና በግልጽ ካስቀመጥነው የሰላማዊ ትግል አቅጣጫችን በተለየ መንገድ መጓዝ የፓርቲውን ሕገ ደንብ በግልፅ መጣስ ከመሆኑም በላይ ከዘመን ዘመን ሲንከባለሉ የመጡ የሃገራችንን የፖለቲካ ችግሮቻችንም ሆነ ህዝባችንን አንገት ያስደፉ እና ለከፋ ድህነት እና ጉስቁልና የዳረጉ ስብራቶቻችንን በማባባስ ሂደት ላይ ከመሳተፍ ተለይቶ አይታይም።

ኢዜማውያን ይህን በውል በመገንዘብ ከሰላማዊ ትግል እና ከዜግነት ፖለቲካ እንቅስቃሴዎች ውጭ ያለን የፖለቲካ እንቅስቃሴ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ መደገፍ፣ የሀሳብም ሆነ የተግባር ተሳትፎም ሆነ ትብብር ማድረግ ከኢዜማዊነት መርኅ ማፈንገጥ መሆኑን ለማስገንዘብ እንወዳለን፡፡

የፓርቲያችን ሊቀመንበር ጉዳይም ከዚህ ከላይ ከተገለፀው መርኅ አንጻር የሚታይ ይሆናል ሲል ፓርቲያችን ይገልፃል።

መስከረም 21/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ


  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
    ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም።… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
    አዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
    ለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
    ቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች
    ቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን ዶላር ሃብት “የሂሳብ… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች
POLITICS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
የመከላከያን ጨምሮ የአሜሪካንን ሚስጢር “ለትውልድ አገሩ አቀብሏል” የተባለው ትውልደ ኢትዮጵያዊ ” ብሄራዊ ጀግና” እየተባለ ነው
በአሜሪካ ብልጽግናን ተክቶ አራት ኪሎ እንዲገባ ” ዳግማዊ ኢህአዴግ” እንደገና እየተበጀ ነው፤ መንግስት ሙሉ መረጃው አለው
Related posts
  • Related posts
  • More from author
POLITICS

ኢራን እኛ ላይ ምን ልታደርግ ትችላለች?

March 28, 2026
POLITICS

አስቸኳይ የአርበኛነት ጥሪ ለኢትዮጵያን

March 4, 2026
POLITICS

ትራምፕ ኢራንን እንደሚወጉ ፍንጭ ሰጡ

January 28, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • INTERVIEW
    • law
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • ያበደው
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2