የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር “ዓለም ይወቃልኝ” ሲል ለተለያዩ አገራት፣ የተባበሩት መንግስታትና አፍሪካ ህብረት እንዲሁም አግባብ ናቸው ላላቸው ተቋማት ያሰራጨውን ደብዳቤ ተከትሎ ኤርትራ ኢትዮጵያን ከሳ መግለጫብ አወጣች።
ፕሬዚዳንት ኢሳያስ የሚመሯት ኤርትራ የኢትዮጵያ መንግሥት “ለጦርነት አጀንዳው ድጋፍ ለማሰባሰብ” ዘመቻ መክፈቱን የሚገልጽ መግለጫ ነው ያወጣጣው።
የኢትዮጵያ መንግስት “ዲፕሎማሲያዊ ዘመቻ አጠናክሮብኛል” ሲል የሚከሳው የኤርትራ መግለጫ፣ የኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ ጨምሮ ለተለያዩ አገር መሪዎች ደብዳቤ ማሰራጨቷን ወቅሷል።
ሐሙስ ሰኔ 19 ቀን 2017 ዓ.ም. የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስቴር ያወጣው መግለጫ፣የሀገሪቱ ኢትዮጵያ “ግጭትን በምክንያት ለማስደገፍ የሐሰት ባንዲራ እያውለበለበች ነው” ሲል ኢትዮጵያን በጸብ ጫሪነት ከሲ ራሱን ንጹህ የሰላም አባት አድርጓል።
ሃዳስ ኤርትራ ላይ የተለተፈው መግለጫ ባለፉት ጥቂት ቀናት ውስጥ የኢትዮጵያ መንግሥት በኤርትራ ላይ ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ዘመቻ ማካሄዱ ገልጾ የከሳ። የዲፕሎማሲያዊ ዘመቻው
“ኤርትራን በተደጋጋሚ ትንኮሳና በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት የግዛት አንድነት ላይ ጥሰቶች መፈጸማቸውን ጠቅሶ የሚወነጅል” እንደሆነ ጠቅሶ ራሱን ለመከላል የሞከረው የኤርትራ መግለጫ ኤርትራ ምንም የጣሰችው ድንበር እንደሌለ፣ በአልጀርሱ ስምምነት መሰረት በተፈቀደላት አካባቢዎች አልይ ብቻ እንደምትንቀሳቀስ አመልክታለች።
የኤርትራ መንግስት በገሃድ ከትህነግ ጋር ግንባር መፍጠሩንና ታጣቂዎችን በማሰለጠን ኢትዮጵያን በመጪው ክረምት ለመውረር በዝግጅት ላይ መሆናቸውን የውጭ ጉዳይ መግለጫ በግልጽ ስም ጠቅሶ ቢከስም የኤርትራ መግለጫ ስም ጠርቶ አላስተባበልም።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ መንግስት የአልጀርሱን የሰላም ስምምነት መቀበሉን ሲገልጽ ወደ ኤርትራ ከተካለሉ ስፋራዎች ወደ ኢትዮጵያ መመለስ ያለባቸው እንዳሉ ቢያስታውቅም በኤርትራ መግለጫ ላይ ይህ አልተካተተም።
“በእሮሚያ ትርምስ ካልተጠረ የሚፈለገው ለወጥ አይመታም” በሚል ሽሬ ላይ ከትህነግ ጋር በተደረገ የጋራ የትግል አቅጣጫ ምክክር መሰረት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ የኢትዮጵያ መንግሥት “የኦሮሞ ሕዝብን የማይወክል የኦሮሙማ አስተሳሰብ” የሚከተል በማስመስል “ኦሮሞነትን” ርዕዮርተ ዓለም በማስመሰል፣ ከሌሎች የአገሪቱ ሕዝብ ጋር ለማጋጨት አጀንዳ መትከላቸው ቁጣ ማስነሳቱ አይዘነጋም። “የኩሽ እና የሴም ግጭት” በማለትን የሰሜንና የደቡብን ሕዝብ በመከፋፈል በቅርቡ በተደረገው የነጻነት በዓል ላይ ማናገራቸውን ተከትሎ ኢትዮጵያዊያን “ኢሳያስ ከኢትዮጵያ ምን ጉዳይ አላቸው” በሚል በየአውዱ መነጋገሪያ አድረገዋቸው የነበረ ቢሆንም በመግለጫው የተባለ ነገር የለም። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቱእር ግን አንስቶታል።
የኢትዮጵያን አየር መንገድ ገንዘብ መስረቅን ጨምሮ በረካታ ጥሰቶችን እንደሚፈጽም ተቋሙና የትግራይ ሕዝብ በተለያዩ አጋታሚዎች ሲገልጹ መቆየታቸው ይታወሳል። የኤርትራ መንግስት በመግለጫው ስለዚሁ ጉዳይ አልተነፈሰም።
ኢሳያስ ንግግራቸው “የኦሮሙማ አስተሳሰብ” በሚል ያነሱት ውንጀላ ” ሳልጠየቅ ስሜ ተካተተ” በሚል ድጋፍ ከሰጡ ፕሮርፌሰር ሕዝቅኤል በስተቀር በርካታ የኦሮሞ ምሁራንን ጨምሮ በብዛት ኢትዮጵያዊያን ተቃውመውታል። ኦሮሞን ለይቶ ለማስጠቃት ታስቦ በዕቅድ ይፋ የሆነው የፕሬዚዳንቱ ንግግር አሁን ላይ በተከታታይ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ላይ ከተጀመረው የእነ ታዬ ደንደአ፣ ገዱ አንዳርጋቸው፣ ልደቱ አያሌው ወዘተ ፍረጃ ጋር ሂን ብሎ የተጋመደ እንደሆነ እየተገለጸ ነው።
የኤርትራ መንግስት ያለ ኢትዮጵያ መንግስት የተዘጉ ድንበሮች ተከፈቱ በሚል በትግራይና አማራ ክልል አዋሳኝ ስፍራዎች ዘለቆ እየገባና መሳሪያ እያጋጋዘ መሆኑ ከትግራይ የዜና እወጃ ይፋ ከሆነ በሁዋላ ነው መንግስት “ዓለም ይወቅልኝ ” ሲል መግለጫ ያወጣው።
“ላለፉት ስድስት አመታት ዝግ የነበረው የዛላንበሳ ድንበር በትናንትናው እለት በይፋ ተከፍቷል። በዚሁ ፕሮግራም ድንበር ላይ የሚገኙ የሁለቱ አገራት ነዋሪዎች በአካል ተገናኝተው ደስታቸውን ሲገልጹ ተስተውለዋል” ዳዊት ከበደ ጁን 12 ቀን 2025 ሰፊ ሃተታ አቅርቧል።
በኢትዮጵያ ህገ መንግስት የመንግስታት ግንኙነት በፌደራል ደረጃ የሚከናወን በመሆኑ የኤርትራ መንግስት በምርጫ ቦርድ ዕውቅና ከተነፈገው ኃይል /ትህነግ ጋር የጀመረው ግንኙነትና ድንበር ዘልቆ በመግባት የሚደረጉ ስምምነቶች ሉ ላዎነትን መጣስ እንደሆነ የህግ ባለሙያዎች ይናገራሉ። መንግስት ይህን ለማስታገስ ኃይል ቢጠቅም ሊያስከሠው እንደማይችል ይናገራሉ።
በለውጡ ማግስት ከተደረገ ስምምነት በኋላ ተከፍተው በድጋሚ የተዘጉ በትግራይ ክልል በኩል ያሉት የዛላምበሳ እና የራማ ድንበር መስመሮች ባለፉት ሳምንት ሲከፈቱ፣ ስጋታቸውን የገለጹ በርካታ ናቸው። ቢቢሲ ድንበሮቹ የተከፈቱት “ከሁለቱም መንግሥታት ይፋዊ ድጋፍ ሳይደረግ በአካባቢው የማኅበራዊ አንቂዎች እና የማኅበረሰብ ተወካዮች አነሳሽነት” እንደሆነ አመልክቶ ፣ “የትግራይ ክልል መንግሥት እና የኤርትራ ባለሥልጣናትንም” ይሁንታ እንደሰጡ ገልጿል። ይህ ዓይነቱ ስምምነት ፍጹም ህገ መንግስቱ የጣሰ እንደሆነ የሚገልጹ የትግራይ ተቃዋሚ ድርጅት አመራሮችና ነዋሪዎች ድርጊቱ አድሮ የትግራይን ሕዝብ ዋጋ እንደሚያስከፍለው ያምናሉ።

