ኦሮሚያ ላይ ተመሳሳይ አቋም እንደሌላቸው የሚታወቁት “የኦሮሞ ልሂቃን” በቅርቡ ሲያትል ተሰብስበው ህብረት መፍተራቸውን በአቋም መግለጫ ቢያስታውቁም፣ አካሄዱ እንደተባለው አለመሆኑን ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ እየገለጹ ነው። አዲስ የብሔር ብሔርሰቦች “ጥምዶ” እንዲመሰርቱ መታዘዛቸውም ተሰምቷል።
የኢትዮሪቪው የዋሽንግቶን ተባባሪ ያሰባሰበውን መረጃ ጠቅሶ እንዳለው በተቃዋሚነት የሚታወቁት የኦሮሞ ተወላጆች አዲስ የብሔር ብሔረሰቦች ቅንጅት እንዲፈጥሩ የታዘዙት በሻዕቢያ ነው። ይህንን እንዲያስፈጽሙ በዋናነት ኃላፊነቱን የወሰዱት ” ጠርናፊ” ፕሮፌሰር ሕዝቅዔል ገቢሳ ናቸው።
” አሁን በስልጣን ላይ ያለውም መንግስትም ሆነ በአማራዎች በኩል የተጀመረው ህብረት የፌደራል ስርዓቱን የሚያከስሙ ናቸው። እኛ የብሄር ብሄርሰቦችን ነጻነት አክብረን በምንፈጥረው ቅንጅት ውስጥ ልትገቡ ይገባል” በሚል በስልክ የተነገራቸው እንዳሉት፣ ይህ ስብስብ በሳምንት ዕድሜ ውስጥ የዙም ስብሰባ ያደርጋል።
የትግራይ ሕዝብ ጦርነት እንደማይፈልግ፣ ከሻዕቢያ ጋር የተደረገውን አዲስ ቅንጅት እንደሚታወቅ ባማስታወቁ፣ የትግራይ ታጣቂ ኃይሎችም በዚሁ ሳቢያ ተከፋፍለው ለሻዕቢያ ስጋት ስለሆኑበት ነው አዲሱ የኦሮሞ ተወላጆ የሚመሩት ጥምረት እንዲቋቋም የተወሰነው።
በስልክና በአካል የደቡብና የምስራቅ ኢትዮጵያን ይወክላሉ የሚሉዋቸውን የዲያስፖራ አባላት በማግባባት ላይ ያሉት ፕሮፌሰር ሕዝቅዔል ገቢሳ፣ በስልክ ላገኙዋቸው “ከሃረሪ፣ ሶማሊያ፣ አፋርና ደቡብ ክልል የተለያዩ ወኪሎችን ስለምንፈልግ ጠቁሙን፣ ወይም ጋብዙልን” ማለታቸውን ጥሪው የደረሳቸው ምስክረነት ሰጥተዋል።
የትግራይ ሕዝብ ብቻ ሳይሆን፣ የኤርትራ ተቃዋሚዎች በአሜሪካ ከኢትዮጵያ መንግስት ተወካዮች ጋር በመሆን የስቴት ዲፓርትመንት ሰዎችን ማግኘታቸውና መምከራቸው በሻዕቢያ ዘንድ እንዲሁም ከሻዕቢያ ጋር የሚሰሩት እነ አቶ ነዓምን ያሉበት ሕብረት ሃዘን ፈጥሯል። እነዚህ አካላት በተደጋጋሚ አሜሪካ እንድታግዛቸው ሙከራ ሲያደርጉ እንደነበር ከራሳቸው ሳይቀር ምስክርነት ሲሰጥበት የቆየ ጉዳይ ነው።
የኤርትራ የዕድሜ ልክ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፉወርቂ በቅርቡ ስለ ኢትዮጵያ በሁለት ክፍል በሰጡት ዲስኩር ከአሜሪካ ጋር አብረው ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ማስታወቃቸው አይዘነጋም። ከእሳቸው መግለጫ በሁዋላ የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር “ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ላኩልን” ባሉት ይፋ ያልሆነ ደብዳቤ፣ አሜሪካ ኤርትራን ልትክስ ቃል መግባቷን ማስታወቃቸው አይዘነጋም።
ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ለዶናልድ ትራምፕ ምርጫ አሸናፊነት “እንኳ ደስ ያለዎ” ሲሉ ለላኩት ደብዳቤ ከዘጠኝ ወር በሁዋላ መልስ ሰጡ ስለተባለለት ደብዳቤ ዋይት ሃውስም ሆነ ራሳቸው ፕሬዚዳንቱ በግል የትሩዝ ገጻቸው የተነፈሱት ነገር የለም።
በወቅቱ የማስታወቂያ ሚኒስትሩን ደብዳቤ ከኤክስ ገጻቸው በመቀባበል የኢትዮጵያ ስም ያላቸው ሚዲያዎችና ታዋቂ ሰዎች ሳይቀሩ “አሜሪካና ኤርትራ ተወዳጁ፣ ብልጽግና አለቀለት” በሚል ተንትነው ነበር፣ ጽሁፍ አጋርተውም እንደነበር አይዘነጋም።
ባለፉት ሳምንታት ከአሜሪካ በይፋ እንደተሰማው የኢትዮጵያ መንግስት ወኪሎችና የኤርትራ ተቃዋሚ ኃይል አመራሮች በአሜሪካ ተገናኝተው መምከራቸው አይዘነጋም። አቶ ጌታቸው ኝኙነቱን በገሃድ ሲያስታውቁ ዝርዝር ጉዳዮችን ባያነሱም በጋራ ከአሜሪካ ባለስልጣናት ጋር በቀይ ባህር ጉዳይና በፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጉዳይ መመከራቸውን የዝግጅት ክፍላችን ታማኝ ምንጮች ገልጸዋል።
ከዚህ በሁዋላ ነው ቀደም ሲል ሶማሊያ፣ ቱርክና ኬንያ በመመላለስ በኢትዮጵያ የምስራቁ ክፍል የትጥቅ ተግል ለማድረግ ከሚደራጁት የኦብነግ መሪዎችና “ተባባሪዎቻቸው” ጋር በመገናኘት ተደጋጋሚ ምክክር እንደሚያደርጉ የሚታወቁት ፕሮፌሰር ሕዝቅዔል ገቢሳ፣ አዲስ የብሄር ብሔረሰቦች ጥምረት እንዲመሰረት የተያዘውን አቅጣጫ እንዲመሩ ሹመት የተሰጣቸው።
ፊልድ ማርሻ ብርሃኑ ጁላ በቅርቡ ለፓርላማ ሲናገሩ በሶማሌ ለአልሸባብ ሲዋጉ የተገደሉና የተማረኩ ኢትዮጵያዊያን መገኘታቸውን መናገራቸው አይዘነጋም። አክለውም “በዚህ ደረጃ ባንዳ ለመሆን የምንመችበትና የምንስማማበት ፍጥነት ያስገርማል። ግብጽ ብትሄዱ አገሩ ላይ የሚማማል ባንዳ አታገኙም” በማለት ግርምታቸውን አካፍለው ነበር።
በጉዳዩ ላይ የግብጽ እጅ እንዳለበት የሚያውቁ እንዳሉት ጉዳዩን በዜና ሽፋን፣ በመናበብ፣ በክፍያ ሰፊ ሽፋን ለመስጠት ከወዲሁ ደፋ ቀና ማለት የተጀመረ መሆኑን አመልክተዋል።
የስብሰባው ጥሪ በስልክ ከደረሳቸው መካከል አንዱ እንዳሉት የኦሮሞዎቹ ስብስብ በራሱ አንድ አቋም የሌለውና አድሮ የሚፈራርስ እንደሆነ አመልክተዋል። ሲያስረዱም “በሕብረታቸው ውስጥ የትህነግ የቀድሞ ወዳጆች አሉ፣ ኢትዮጵያን ቅኝ ገዢ አድርገው የሚፈርጁና ነጻ ኦሮሚያ የሚሉ አሉ። በየቀኑ የሚገላበጡና አመጽና ሁከት ባለበት ሁሉ የሚቆሰቁሱ አሉበት። እነዚህ ታዲያ እንዴት አድርገው ነው ሁሉን የሚያካትት አዲስ ፌደራሊዝም ሊመሰርቱ የሚችሉት?” በሚል አስበውበት ሌሎች ሳይሳሳቱ ቆም ብለው እንዲያስቡ ቢጠቅም በሚል እሳቤ መረጃውን ማካፈላቸውን ጠቁመዋል።
በአሜሪካ የአሜሪካ ሬዲዮ ኃላፊ የነበሩት አቶ ንጉሴ አክሊሉ የሚመሩት ቪዝን ኢትዮጵያን ጨምሮ በርካታ ህብረት፣ የብሄር ማህበሮች፣ ጥምዶዎችና ” እንዲህ ብሎኝ ነበር” በሚል በመናበብ ፕሮፓጋንዳ የሚሰሩ በርካታ የማህበራዊ ሚዲያ አውታርና የዩቲዩብ ገጾች እንደሚገኙ ይታወቃል።
የኦሮሞ ተወላጅ ምሁራን ያቋቁሙታል የተባለው የብሔር ብሔረሰቦች “ጥምዶ” ስሙ እስካሁን በይፋ አልታወቀም። ስሙ ባይታወቅም በሳምንት ጊዜ ውስጥ የዙም ስብሰባ በማድረግ ወደ መድረክ ብቅ እንደሚል መረጃውን ያካፈሉት አስታወቀዋል።
ይህ “ጥምዶ” ይፋ ሲሆን ከለውጡ በሁዋላ ትህነግ ካቋቋመው “የፌደራል ኃይሎች” እና አቶ ልደቱ ከሚመስሉትና ከትግራይ ኃይሎች ጋር በመሆንካቋቋመው ሕዝብረት ቀጥሎ ሶስተኛው ይሆናል።

