Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  ጸደይ ባንክ 870 ሚሊዮን ብር ከሰረ፤ “በባንኩ ቅርንጫፎች ገንዘብ ሲኖር ዘራፊዎች መረጃ ይደርሳቸዋል”
News

ጸደይ ባንክ 870 ሚሊዮን ብር ከሰረ፤ “በባንኩ ቅርንጫፎች ገንዘብ ሲኖር ዘራፊዎች መረጃ ይደርሳቸዋል”

Ethioreview newsEthioreview news—August 20, 2025
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የአማራ ክልል የልማት ድርጅቶች ከሚባሉት መካከል አንዱ የሆነው የጸደይ ባንክ በዓመቱ መጨረሻ 870 ሚሊዮን ብር ከስሯል። የኢትዮሪቪው ተባባሪ ከባህር ዳርና አካባቢው ባሰባሰበው መረጃ ባንኩን ያከሰረው ዝርፊያ ነው። በባንኩ ቅርንጫፎች ገንዘብ ሲኖር ዘራፊዎች መረጃ እንዲደርሳቸው ይደረጋል።

ስማቸውን ለመግለጽ የሚፈሩና በሚፈጸመው ነወር ተግባር ማዘናቸውን የገለጹ እንዳሉት የጸደይ ባንክ በፍጹም ሊከስር አይችልም። ባንኩ የክልሉ ሃብት በመሆኑ በክልሉ በስፋት እስከ ገጠር ድረስ የተዘረጋ፣ የየአካባቢው የክልሉ መንግስት የአስተዳደር መዋቅር ድጋፍ የሚያደርግለት ተቋም ስለሆነ ኪሳራ ከቶውን የሚታሰብ እንዳልሆነ እነዚሁ ወገኖች ያስረዳሉ።

ለሃያ ስድስት ዓመታት የአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም በሚል ስያሜ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው ተቋም ፀደይ ባንክ ተብሎ ወደ ባንክነት አድጎ ስራ የጀመረው በመስከረም 2015 ነበር።

በባንኩ ይፋዊ ስራ ማስጀመሪያ ስነ ስርዓት ላይ የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር፣ የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ዶክተር ይልቃል ከፋለ ፣የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይና የብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር ይናገር ደሴ ተገኝተው እንደነበር በወቅቱ መዘገቡ አይዘነጋም።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

ከአገር እስኪወጡና በይፋ የፋኖ ትግልን መቀላቀላቸውን እስካሳወቁ ድረስ የባንኩ የቦርድ ሊቀመንበር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ነበሩ። በማስጀመሪያው ስነ ስርዓ ላይ ይፋ እንደሆነው በ2015 ባንኩ አስራ ሁለት ሚሊዮን ደንበኞችና 500 ቅርንጫፎች ነበሩት።

አሁን ላይ ደግሞ ፀደይ ባንክ ከ60 ቢሊዮን ብር በላይ አጠቃላይ ሃብት፣ ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ አጠቃላይ ካፒታል እና ከ9 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ የተከፈለ ካፒታል ያለው ግዙፍ ባንክ እንደሆነ በባንኩ ድረገጽ ላይ እ እ አ በኦክቶበር 2024 ፕሬዚዳንቱን አቶ መኮንን የለውምወሰን ጥቅሶ ጽፏል። ከ627 በላይ በሚሆኑ ቅርንጫፎቹም በመላ ሃገሪቱ ከ14 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ የቁጠባ እና ከ1 ሚሊዮን በላይ የብድር ደንበኞችን እያገለገለ እንደሚገኝም አብሮ ተመልክቷል።

መረጃ ያጋሩን እንደሚሉት በዚህ ደረጃ ያለ ባንክ በፍጹም ሊከስር እንደማይችል ነው። ከደንበኞች አገልግሎት ባለፈ ለሌሎች ባንኮች ብር የሚያበድረው ጽደይ ባንክ፣ ብድር ለመስጠት፣ የሰጠውን ብድር ለመሰብሰብ ችግር እንደሌለበትም እነዚሁ ምንጮች ይገልጻሉ። ጥያቄያቸው የመንግስት መዋቅሮች በሙሉ ያበደረውን የሚሰበስቡለት፣ ወይ እንዲሰበስብ ድጋፍ የሚያደርጉለት ባንክ የከሰረው ከውስጥ መረጃ የሚያቀብል በመኖራቸው እንደሆነ ይገልጻሉ።

ዛሬ ላይ የቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት የቀድሞ የባህር ዳር ከተማ አስተዳስደር ከንቲባና አሁን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ድረስ ሳህሉ መሆናቸውን የሚጠቁሙት እነዚህ ክፍሎች እሳቸውም ሆኑ የባንኩ የበላይ ኃላፊዎች ለኪሳራው ሊሰጡ የሚችሉት በአመክንዮ የሚደገፍ ምክንያት እንደማይኖራቸው ገልጸው ባንኩ በዝርፊያ የሕዝብ ሃብት እንዳጣ ይገልጻሉ።

በአማራ ክልል ሁለት ቦታ የሚጫወቱ እንዳሉ በስፋት ይገለጻል። መከላከያ እርምጃ ሊወስድ ሲል ሳይቀር አስቀድመው መረጃ የሚያሾልኩ መኖራቸውን ሕዝብ አደባባይ የሚመሰከረው ጉዳይ እንደሆነ ተባባሪያችን ከላከው ሪፖርት ለመረዳት ተችሏል።

እገታ፣ አፈናና ዝርፊያ እጅግ በተስፋፋበት ወቅት መዋቅር ውስጥ የዘለቀ እርምጃ ሲወሰድ ችግሩ ተቃሎ እንደነበር የሚናገሩ የባህር ዳር ነዋሪዎች፣ አንድ ባለስልጣን ከዚሁ ወንጀል ጋር በተያያዘ በጸጥታ ኃይሎች ሲያዙ ወደ አዲስ አበባ አንድ ክልሉ ላይ ተጽዕኖ ለሚፈጥሩ ከፍተኛ ባለስልጣን ወዲያው በመደወል እንዲለቀቅ መደረጉንና ይኸው ሰው አሁን ድረስ በኃላፊነቱ ላይ እንደሚገኝ ስም ጠርተው ነዋሪዎች ይናገራሉ።

ከጸደይ ባንክ መረጃ ያላቸው እንደሚሉት ባንኩ በዝርፊያ ለኪሳራ የተዳረገው የትኞቹ ባንኮች ላይ ገንዘብ እንዳለ አስቀድሞ ለታጣቂዎች መረጃ በውመስጠት ነው። መረጃ የሚደርሳቸው ታጣቂዎች ባንኩን በተደጋጋሚ እንደዘረፉት የሚያመለክቱ ምንጮች ዘረፋው የተለመደ መሆኑን ያመለክታሉ። በዜናም እንደሚዘገብ ይገልጻሉ።

በጸደይ ባንክ ብቻ ሳይሆን በተለያዩ የአገሪቱ ክፍል በነጻ አውጪነትና በትግል ስም መሳሪያ አንግበው በሚዲያ ድጋፍ የሚደረግላቸው አብዛኞቹ “ስራ” እያሉ የሚጠሩት በዝርፊያ የመክበር ጉዳይ ነው። ከተለያዩ አካባቢዎች የሚሰሙ አቤቱታዎች እንደሚመሰክሩት ጫካ ሆነው ሃብት ያከማቹ ጥቂት አይደሉም።

መዋቅር ውስጥ ካሉ ኃላፊዎች ጋር በመቀናጀት እንደሚፈጸም የሚነገርለት ይህ ሕዝብን ግራ ያጋባ ዘረፋ የሚጠራበት አጋባብ ካልተፈጠረ ወደፊት ችግሩ ሰፊ አገራዊ መዘዝ ሊያስከትል እንደሚችል ጉዳዩ ያሳሰባቸው ደጋግመው ሲወተውቱ እየተደመጠ ነው። ራሱ ገዢው ፓርቲ በሁለት ካባ መጫወት እንደማይቻል ባስታወቀበት የሰሞኑ መግለጫው ውስጡን እንደሚያጠራ ሲያስታውቅ ችግሩን አምኖ ነበር።


NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
የአሲይቲ ፓርክ ኃላፊዎች እስር የመንግስት ሹመኖች መጠቃቃት? “መንግስት ባስቸኳይ አጥርቶ እርምጃ ይውሰድ” – ልዩ ሪፖርት
የኦሮሞ ብሄርተኞች አዲስ የብሄረሰቦች “ጥምዶ” በትዕዛዝ መሰረቱ፤ ሕዝቅዔል በጠርናፊነት ተሹመዋል
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2