ኢትዮሪቪው ፡- ከጥር 10 ቀን 2018 ጀምሮ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዢ ሆነው ላበረከቱት አስተዋጾዖ እያመሰገንኩ ከነሃሴ 28 ቀን 2017 ጀምሮ ከኃላፊነት የተነሱ መሆኑን አስታውቃለሁ” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አስታወቁ። አቶ ማሞ በግል የኤክስ ገጻቸው ከመንግስት ስራዎችና ኃላፊነታቸው በገዛ ፈቃዳቸው መልቀቃቸውን “የምስጋናና የስንብት መልዕክት” በሚል በጻፉት ደብዳቤ ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዢ አቶ ማሞ ምሕረቱ “የምስጋናና የስንብት መልዕክት” በሚል ርዕስ በግል ኤክስ ገጻቸው በቀጣይ የሕይወት ዘመናቸው በሌላ ኃላፊነት ለመቀጠል በሚል ወደ ዓለም ዓቀፍ ተቋማት እንደሚያመሩ ፍንጭ ከሰጡ በሁዋላና ከመንግሥታዊ አገልግሎት የሚወጡበት ጊዜ መድረሱን በመጠቆም ኃላፊነታቸውን መልቀቃቸውን አስታውቀዋል።
አቶ ማሞ ምሕረቱ በግል የቲውተር ገጻቸው ከኃላፊነታቸውና ከመንግስት ስራ መልቀቃቸውን ማስታወቃቸውን ተከትሎ ስለቀጣይ ኃላፊነታቸው ምንም የተባለ ነገር የለም። ይሁን እንጂ ከስራ ለመልቀቅ ያቀረቡትን ማመልከቻ መንግስት መቀበሉ ግልጽ መሆኑ ተሰምቷል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥና የቀድሞ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ማሞ ምህረቱ ለሰባት ዓመታት ያገለገሉበትን የመንግስት የስራ ሃላፊነት መልቀቃቸውን አስታወቁ።
አቶ ማሞ ከስልጣን መልቀቃቸውን ባሳወቁበት መልዕክታቸው፣ በመንግስት ውስጥ በተለያዩ የስራ ሃላፊነቶች ማገልገላቸው ትልቅ ክብር እንደሆነ ገልጸዋል።
በተለይም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በመሩት የቤት-አስተዳደር ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም ውስጥ በመስራታቸው እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክን በገዥነት መምራታቸው ከፍተኛ እርካታ እንዳስገኘላቸው ገልጸዋል።
በብሔራዊ ባንክ ቆይታቸው፣ ባንኩን ከ50 ዓመታት በኋላ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች እንዲያከናውን መምራታቸውን አብራርተዋል።
ከቡድን አጋሮቻቸው ጋር በመሆን ዘመናዊ የገንዘብ ፖሊሲ ማዕቀፍን ተግባራዊ ማድረጋቸውን፣ ወደ ገበያ-ተኮር የውጭ ምንዛሪ ስርዓት መሸጋገራቸውን እና የባንኩን ነጻነት የሚያረጋግጥ አዲስ ህግ መውጣቱን አስታውሰዋል። አቶ ማሞ
- በዓለም ባንክ ውስጥ በከፍተኛ ባለሙያነት
- የጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፍተኛ የምጣኔ ሃብት አማካሪ
- የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆሊዲንግስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ
በተጨማሪም የፋይናንስ ዘርፉን ለውጭ ባንኮች ክፍት ማድረጋቸውን፣ ዲጂታል ክፍያን ማስፋፋታቸውን እና 10.58 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ፋይናንስ ማስገኘታቸውን በዝርዝር አስቀምጠዋል።
አቶ ማሞ ይህንን የስራ እድል የሰጣቸው እና የመራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ መሆናቸውን በመግለጽ ምስጋና አቅርበዋል። አቶ ምህረቱ ወደ ዓለም ዓቀፍ ድርጅት ሊዛወሩ እንደሚችሉ ፍንጭ የሰጡ ሲሆን፣ የሚቀርቧቸውም ይህንኑ እየገለጹ ነው። ጠላይ ሚኒስትር አብይ መሰናበታቸውን ከመግለጽ ውጭ ሌላ ያሉት ነገር የለም።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ለአቶ ማሞ ምስጋናውን አቅርቦ ለቀጣይ የስራ ዘመናቸው ስኬት መመኘቱን ገልጾ አጭር መልዕክት በይፋ አሰራጭቷል። አቶ ማሞ ዶክተር ይናገር ደሴን እንደተኳቸው ይታወሳል።


