Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  የኢሳያስ ዕቅድ እንደሆነ የተነገረለት ወረራ በአፋር ክልል ተፈጸመ፤ አፋር ክልል “ራሴን እከላከላለሁ” አለ
News

የኢሳያስ ዕቅድ እንደሆነ የተነገረለት ወረራ በአፋር ክልል ተፈጸመ፤ አፋር ክልል “ራሴን እከላከላለሁ” አለ

Ethioreview newsEthioreview news—November 7, 2025
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

አዲስ ሪፖርተር – በአፋር ክልል ተጀመረ የተባለው ወረራ፣ “የፌደራል ስርዓቱን እናፈርሳለን” በሚል ወታደራዊ ዝግጅቱን እያጠናከሩ ያሉት የፕሬዚዳንት ኢሳያስ ዕቅድ መሆኑን አቶ ጌታቸው ረዳ አመለከቱ። በአፋር ክልል ላይ የተጀመረውን ወረራ አስመክቶ “እናንተ ኋላ ቀር ቡድኖች ወደ አፋር የሚወስደውን መንገድ በመዝጋት የአፋርን ህዝብ እንደ መደራደሪያ መሳሪያ ለመጠቀም ፍላጎት እንዳላችሁ አውቃለሁ” ሲሉ አቶ ጌታቸው አስታውቀዋል። ድርጊቱንም “ክህደት” ብለውታል። የአፋር ክልል ራሱን ለመከላከል እንደሚገደድ አስታውቋል። ከመንግስት ወገን የተባለ ነገር የለም።

የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ፈረሰ፤ በአፋርን ስድስት መንደሮች ተወረሩ፤ መንግስት የውጊያ ግብዣ ቀረበለት

ከአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ወረራ መካሄዱን ተከትሎ ባወጣው መግለጫ “ካለፉት ጥፋቶች መማር ያልቻለ” በማለት በእነ ዶክተር ደብረጽዮን የሚመራውን የትህነግ አንድ ክፋይ ይከሳል።  አክሎም

“ከጥፋቱ የማይመረው ጉጅሌው የትህነግ ቡድን በ26/02/2018 ዓ.ም በአፋር ክልል ወሰን ውስጥ በማግባት ስድስት መንደሮችን በጉልበት በመቆጣጠር ንጹሃንን በሞርታርና በዙ-23 በመደብደብ የተለመደውን የሽብር ተግባሩን በግልጽ ጀምሯል” ሲል ክስ ያሰማበትን ምክንያት ያስረዳል።  

“ኋላ ቀር የሆነው ቡድን የፕሪቶሪያን ስምምነት ለማፍረስ የተለያዩ ትንኮሳዎችን ሞክሯል። ነገር ግን የፌደራል መንግስቱ ታግሷል” ሲሉ በትግርኛ ቋንቋ በግል ኤክስ ገጻቸው አቶ ጌታቸው አስጠንቅቀዋል።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

አቶ ጌታቸው እንደወትሮው ትንኮሳው ሕዝብን ለመጫፍጨፍና ለስቃይ ለመዳረግ የተደረገ መሆኑን አመክልክተው፣ ወረራውን “ አሁንም የፌዴራል መንግስትን ጎትቶ ወደ ግጭት ለማስገባት በአፋር ክልል ትንኮሳ ፈፅሟል። ይህ የሻቢያ አጀንዳን ለማስፈፀም የሚደረግ እንቅስቃሴ ነው፣ለዚህ ዋና ተጠያቂዎቹ ፍሳሃ ማንጁስ እና ዮሐንስ ናቸው” ብለዋል።

የአፋር ክልላዊ መንግስት መግለጫው “አዛውንቶቹ” ሲል የጠራቸውን እነዚህኑ ክፍሎች፣ “የህወሓት ጉጅሌ በአፋር ክልል በዞን ሁለት በመጋሌ ወረዳ ቶንሳ ቀበሌ ዋራዓ እና ሚልኪ በሚባሉ ልዩ አካባቢዎች ወሰን ተሻግሮ በመግባት ከምሽቱ አንድ ሰዓት አካባቢ በንጹሐን የአፋር አርብቶ አደሮች ላይ የከባድ መሳሪያ ተኩስ በመክፈት የፕሪቶሪያ ስምምነትን በግጭት አዋጅ በግልጽ አፍርሷል” በማለት ጦርነት መታወጁን አስታውቋል።

“ይህ የህወሓት ጣባጫሪ ቡድን በቶንሳ ቀበሌ ላይ ተኩስ በሚከፈትበት ወቅት ሰላም ወዳድ የአፋር ሽማግሌዎች እንዲመለሱ ቢማፀኗቸውም ጉጅሌው ግን አሻፈረኝ ብሏል” ያለው የአፋር ክልል መግለጫ፣ የአዛውንቶችን ተማጽኖ ወደ ጎን በመተው ጥፋት መፈጸሙን አመልክቷል።

መግለጫው እንዳለው “ይህ ከትናንት ጥፋቱ የማይማረው ተስፋ ቢሱ የህወሓት ጉጅሌ ቡድን ከድርጊቱ በአስቸኳይ ካልተቆጠበ የአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት የዜጎች ደህንነትና የወሰኑን ክብር የማስጠበቅ፣ እንዲሁም ራስን ከማንኛውም ውጫዊ ጥቃት የመከላከል ኃላፊነቱን እንደሚወጣ እንገልፃለን” ሲል ማሳሰቢያ ሰጥቷል።

አቶ ጌታቸው “ምክር” ሲሉ ባሰራጩት ጹፋቸው፣ የአፋርን ስድስት ቀበሌዎች ወሯል የተባለውን ቡድን “ይህ እንቅስቃሴ ለህዝቡ ስቃይ ለማምጣት እና ህዝቡን ለመጨፍጨፍ የሚደረግ የክህደት እንቅስቃሴ ነው” ብለውታል።

“እናንተ ኋላ ቀር” አሉ አቶ ጌታቸው “እናንተ ኋላ ቀር ቡድኖች ወደ አፋር የሚወስደውን መንገድ በመዝጋት የአፋርን ህዝብ እንደ መደራደሪያ መሳሪያ ለመጠቀም ፍላጎት እንዳላችሁ አውቃለሁ” ሲሉ አስቀድመው የሚያውቁትን ሚስጢር ይፋ አድርገዋል።

“ይህ እንዲሆን በፍፁም አታስቡ” አሉ አቶ ጌታቸው አከሉና  “የትግራይ ጦር (TDF እና TPF) ትግራይን ከፌዴራል መንግስት ጋር በምንም መልኩ የሚያጋጭ አጀንዳ የላቸውም። ስለዚህ ይህ ኋላ ቀር ቡድን የሻቢያ አጀንዳ መጠቀሚያ እንዳይሆን መታገል ያስፈልጋል” ሲሉ ሁሉም ወገኖች ሊይዙት የሚገባውን አቋም አስታውቀዋል። ብለዋል። የአፋርን ክልል ዘልቆ የገባው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ጦር አንድ ክፋይ በወረራ ያዛቸው የተባሉት ቀበሌዎች ወርዓ፣ ኩስ ሰበበራ፣ ዶያ፣ ገደ ባለዓ፣ ካርማ ኣጋና ሚልኪ መሆናቸው ታውቋል።

በሌላም አቅጣጫ የከባድ መሳሪያ ልውውጥ እንደሚሰማ ምስክሮች እያስታወቁ ነው። የአፋር የፀጥታ ኃይሎችም ሆነ መከላከያ በግልጽ ምላሽ መስጠት ስለመጀመራቸው የተባለ ነገር የለም። ይሁን እንጂ ክልሉ ወረአውን ለመከላከል እንደሚገደድ ባስታወቀው መሰረት ኃይሉን ማዘጋጀቱ ታውቋል።

በዶክተር ደብረጽዮን የሚመራው ትህነግ ይህ እስከተጻፈ ድረስ ያለው ነገር የለም። አስቀድሞ ግን የፌደራል መንግስት የፕሪቶሪያውን ስምምነት አፍርሷል በሚል ክስ አቅርቦ ነበር።

እነ ዶክተር ደብረጽዮንና ሻዕቢያ የፈጠሩትን ጥምረት የሚቃወሙና እዛው መካከላቸው ያሉት መኮንኖችም ይሁን ተዋጊዎች ወደ አፋር ክልል የገባውን ሰራዊት አስመልክቶ ለማነጋገር ሙከራ ብናደርግም አልተሳካም።  

foto file


NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
የብር እርሻ – ስደተኛው ፋኖ “ገንዘብ በእህል ሚዛን እየተካፈሉ ነው” ስራ ብዙው የሰመራ ኢምግሬሽን የአሻራ ክፍያ
በኢትዮጵያ ነብሰ ገዳዮችን ለምን ኃላፊነት አይወስዱም?” የንጹሃን ግድያ በፖለቲካ እየተሰላ እስከመቼ?
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2