እየተወሰደ ባለው ሕግ የማስከበር እርምጃ በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ከ1 ሺህ በላይ ተጠርጣሪዎች ለሕግ ቀረቡ፡፡ እየተወሰደ ባለው ሕግ የማስከበር እርምጃ 1 ሺህ 1 መቶ 13 ተጠርጣሪዎችን ለሕግ ማቅረቡን የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር አስታወቀ።
ከተጠርጣሪዎቹ መካከል 130 የሚሆኑት በሰው ነፍስ ማጥፋት ወንጀል ተጠርጥረው በህግ ሲፈለጉ የነበሩ ናቸው ተብሏል፡፡
የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንግዳ ዳኛው በብሔረሰብ አስተዳደሩ በቡድንና በተናጠል የተደራጁ ኀይሎች የኅብረተሰቡን መደበኛ እንቅስቃሴ በማስተጓጎል ሕዝቡ በመንግስት ላይ አመኔታ እንዳይኖረው ሲሰሩ መቆየታቸውን ተናግረዋል፡፡
የሕግ የበላይነት እንዲከበር ከኅብረተሰቡ በተነሳው ብርቱ ጥያቄና በመንግስት ቁርጠኝነት በተወሰደ እርምጃ እስካሁን ድረስ በብሔረሰብ አስተዳደሩ 1ሺህ 1መቶ 23 የወንጀል ተጠርጣሪዎች ለህግ ማቅረብ ተችሏልም ብለዋል ዋና አስተዳዳሪው፡፡
በቁጥጥር ስር ከዋሉት የወንጀል ተጠርጣሪዎች መካከል 130 የሚሆኑት በነፍስ ማጥፋት ወንጀል ተጠርጥረው በህግ ሲፈለጉ የነበሩ ሲሆን ቀሪዎቹ በመግደል ሙከራ፣ በተደራጀ ዝርፊያ፣ በህገ ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በአስገድዶ መድፈርና በልዩልዩ ወንጀሎች የተጠረጠሩ መሆናቸውን ዋና አስተዳዳሪው ተናግረዋል፡፡
በፀጥታ ኀይሎች ላይ ጥቃት ለማድረስ ከሞከሩ ውስን ተጠርጣሪዎች በስተቀር በህግ ጥላ ስር የሚገኙ ሁሉም ተጠርጣሪዎች ሰብዓዊ መብታቸው ተጠብቆ ተገቢውን የፍርድ ውሳኔ እንዲያገኙ በየደረጃው በሚገኙ የወረዳ አስተዳዳሪዎች የሚመራ ግብረ ኀይል ተቋቁሙ እየተሰራ ስለመሆኑንም ገልፀዋል፡፡
ህግ የማስከበር እርምጃው የታሰበውን ግብ ሙሉ በሙ አሳክቷል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ኅብረተሰቡ በህግ የሚፈለጉ የቤተሰብ አባላትን ሳይቀር አሳልፎ በመስጠት ለህግ የበላይነት በከበር ቁርጠኝነቱን አሳይቷል ብለዋል፡፡
ህግ የማስከበር እርምጃው ኅብረተሰቡ በሰላም ወጥቶ በሰላም የመግባት ነፃነቱን እስኪጎናፀፍ ድረስ ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው የብሔረሰብ አስተዳደሩ ሕዝብ ተጨማሪ ተጠርጣሪዎችን ለህግ ለማቅረብ በሚደረገው ጥረት የተለመደ ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል ፡፡
ዘጋቢ፦ሳሙኤል አማረ – አሚኮ
- 𝐄𝐭𝐡𝐢𝐨𝐩𝐢𝐚 𝐑𝐞𝐚𝐟𝐟𝐢𝐫𝐦𝐬 𝐖𝐓𝐎 𝐀𝐜𝐜𝐞𝐬𝐬𝐢𝐨𝐧 𝐂𝐨𝐦𝐦𝐢𝐭𝐦𝐞𝐧𝐭 𝐚𝐭 𝐆𝐞𝐧𝐞𝐫𝐚𝐥 𝐂𝐨𝐮𝐧𝐜𝐢𝐥 𝐌𝐞𝐞𝐭𝐢𝐧𝐠State Minister of Finance, Eyob Tekalign, delivered a strong statement at the WTO General Council meeting, reaffirming Ethiopia’s unwavering commitment… Read more: 𝐄𝐭𝐡𝐢𝐨𝐩𝐢𝐚 𝐑𝐞𝐚𝐟𝐟𝐢𝐫𝐦𝐬 𝐖𝐓𝐎 𝐀𝐜𝐜𝐞𝐬𝐬𝐢𝐨𝐧 𝐂𝐨𝐦𝐦𝐢𝐭𝐦𝐞𝐧𝐭 𝐚𝐭 𝐆𝐞𝐧𝐞𝐫𝐚𝐥 𝐂𝐨𝐮𝐧𝐜𝐢𝐥 𝐌𝐞𝐞𝐭𝐢𝐧𝐠
- ❝የአሸባሪውና ወራሪ የመጨረሻ ግብዓተ መሬት የምንፈፅምበት ጊዜ ሩቅ አይደለም❞ ጄነራል ብርሃኑ ጁላ❝እኛ የምንዋጋው ኢትዮጵያን ለማዳን ነው፤ የሕልውና ጦርነት ነው፤ ጠላት የሚዋጋው ኢትዮጵያን ሊያፈራርስ ነው፤ ከአማራ ላይ ሒሳብ ሊያወራርድ ነው፤ የውጭ ኮሪደር… Read more: ❝የአሸባሪውና ወራሪ የመጨረሻ ግብዓተ መሬት የምንፈፅምበት ጊዜ ሩቅ አይደለም❞ ጄነራል ብርሃኑ ጁላ
- ❝በሴራ ልክፍት እየናወዙ የለውጡ አካል ሆኖ መቀጠል አይቻልም!❞ የአማራ ብልጽግና ፓርቲየአማራ ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት በወቅታዊ ጉዳይ ባስተላለፈው መልዕክት ❝በሴራ ልክፍት እየናወዙ የለውጡ አካል ሆኖ መቀጠል አይቻልም!❞ ብሏል። ፓርቲው ከልወጡ… Read more: ❝በሴራ ልክፍት እየናወዙ የለውጡ አካል ሆኖ መቀጠል አይቻልም!❞ የአማራ ብልጽግና ፓርቲ





