አሜሪካ ታይዋንን ከቻይና ወረራ ለመጠበቅ ኃይል ልትጠቀም እንደምትችል ማስታወቋን ተከትሎ ቻይና “ለአሜሪካ ከባድ ማስጠንቀቂያ ነው” ያለችውን ወታደራዊ ልምምድ በታይዋን አቅራቢያ ማድረጓን የሀገሪቱ ጦር አስታውቋል።
የቻይና ጦር ቃል አቀባይ በትናትናው እለት እንዳስታወቀው፤ ቻይና እራሷን በራስዋ የምታስተዳድር ደሴት ላይ ያላትን ቁርጠኝነት ለአሜሪካ ለማሳየት በቅርቡ በታይዋን አቅራቢያ ተከታታይ ወታደራዊ ልምምዶችን አድርጋለች።
የቻይና ጦር የምስራቃዊ እዝ በታይዋን ዙሪያ የውጊያ ዝግጁነት ልምምዶችን እና ሌሎች የስልጠናዎችን በባህር እና አየር ላይ ማካሄዱንም የወታደራዊ እዙ ቃል አቀባይ ኮሎኔል ሺ ዪ ተናግረዋል።
ልምምዱ አሜሪካ ለታይዋን እውቅና ለመስጠት እያደረገችው ላለው እንቅሰቃሴ “ከባድ ማስጠንቀቂያ” መሆኑንም ቃል አቀባዩ ገልፀዋል።
ታይዋን የግዛቴ አንድ አካል ናት የምትለው ቻይና በታይዋን ጉዳይ ከአሜሪካ ጋር ጭምር በተደጋጋሚ ግጭት ውስጥ ስትገባ ይታያል።
ባሳለፍነው ሳምንት በእስያ ጉብኝት ያደረጉት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ኀገራቸው ታይዋንን ለመጠበቅ ኃይል ልትጠቀም እንደምትችል መናገራቸው ይታወሳል።
ባይደን ቻይና ታይዋንን በተመለከተ ኃይል የምትጠቀም ከሆነ እኛም መጠቀማችን አይቀርም ብለዋል፤ የንሰጠው መልስ ለሩሲያ እንደሰተነው አይደለም ሲሉ መናገራቸው ይታወሳል። በጋዜጣ መግለጫቸው ወቅት ጠያቂው ደግሞ ሲጠይቃቸው ” አዎ ወታደራዊ እርምጃ እንወስዳለን” ብለዋል።
የቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ጅንፒንግ ከወራ በፊት ታይዋንን ከቻይና ጋር ለማዋሃድ መዛታቸው የሚታወስ ሲሆን፤ ፕሬዝዳንቱ ለማዋሃድ ኃይል መጠቀም ስለማሰባቸው አልተናገሩም። ታይዋን ነጻ ሀገር ነኝ የምትል ሲሆን፤ በአንጻሩ ቻይና ታይዋንን የግዛቷ አካል አድርጋ ትመለከታታለች። በቅርቡ የተዋሃዱ አገር እንደሚሁኑ አስታውቃለች። ዜናው ከአል አይን የተደበላቀ ነው።
- President Taye champions Africa’s dev’t and regional transformation with GERD at UNGA 80In a comprehensive address to the 80th session of the United Nations General Assembly in New York, President… Read more: President Taye champions Africa’s dev’t and regional transformation with GERD at UNGA 80
- Two African countries refuse to recognise Palestine. Here’s whyAt the United Nations General Assembly this week, one country after another rose to declare its recognition of… Read more: Two African countries refuse to recognise Palestine. Here’s why
- UN Chief Stresses Need for Countries to Adopt Climate-smart Food Policies to Reduce Reliance on Food ImportsUN Secretary-General Antonio Guterres stressed the need for countries to adopt climate-smart food policies and enhance private sector… Read more: UN Chief Stresses Need for Countries to Adopt Climate-smart Food Policies to Reduce Reliance on Food Imports




