Skip to content
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  Monday 18 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • Home Demo news
  • News
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    በጦርነቱ ጉዳት ለደረሰባቸው ባለሀብቶች ብድር ከመስጠት አንስቶ ሌሎችም ድጋፎች እንደሚሰጥ ተገለፀ፡፡

    February 9, 20220

    ሹፌሮችን በመግደል ተሽከርካሪ ሲሰርቁ የነበሩ አራት ግለሰቦች የሞት ቅጣት ተወሰነባቸው

    October 21, 20240

    የአማራ ክልል ከትግራይ ጋር ሁሉንም ጉዳይ በውይይትና በሰላማዊ መንገድ ለመጨረስ ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ

    March 31, 20230

    Sudan official: ‘Mediation between Khartoum and Addis Ababa faces obstacles’

    February 14, 20210
    Prev Next Showing 1 Of 1866
  • Design
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    መላው አማራ ከነገ ጀምሮ ለህልውና ዘመቻ እንዲነሳ ክተት ተጠራ

    July 25, 20210

    የጆ.ባይደን አስተዳደር የሰላም አማራጭ ንግግሩን ቀድሞ የትህነግን ፍላጎት አቋም አድርጎ አቀረበ

    November 1, 20220

    በሽረ አዲስ ተስፋ፤ ሕዝብ በነጻነት ስለቀጣዩ ዕጣው አየመከረ ነው

    December 26, 20220

    እውነትን ለሥልጣን መናገር ፣ ሳማንታ ፖወር ለኢትዮጵያ ዘር ፖለቲከኞች መከላከል አቁሚ!

    March 1, 20210

    በአዲስ አበባ ከ27ሺህ በላይ ወጣቶች ተደራጅተው ከተማዋን እየጠበቁ ነው

    November 11, 20210
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • Video
    video

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ለፓርላማ የሰጡት ማብራሪያ

    July 4, 2024
    video

    የህብታቸውን ምንጭ የሚያውቁ አይሰጉም! ማብራሪያ

    June 22, 2024
    video

    የሀገር አቀፍ የምክክር ሂደት ይፋዊ የማስጀመሪያ ሥነ ስርዓት

    June 4, 2024
    video

    የምክክር ሂደት ይፋዊ ማስጀመሪያ ላይ ያደረጉት ሙሉ ንግግር

    June 4, 2024
    Prev Next Showing 1 Of 5
  • Categories
    • News
      • Europe
      • Politics
        • Reaction
          • Feedbacks
          • Opinions
            • Poeple
            • Reports
      • US
      • World
    • Design
      • Architecture
      • Devices
      • Inspiration
      • Trends
    • Events
      • Movies
      • Music
      • Social media
      • Stars
    • Featured
      • Lifestyle
      • Technology
      • Tourism
      • Travel
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • News
  • Design
  • Video
  • Categories
    • News
      • Europe
      • Politics
        • Reaction
          • Feedbacks
          • Opinions
            • Poeple
            • Reports
      • US
      • World
    • Design
      • Architecture
      • Devices
      • Inspiration
      • Trends
    • Events
      • Movies
      • Music
      • Social media
      • Stars
    • Featured
      • Lifestyle
      • Technology
      • Tourism
      • Travel
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • Home Demo news
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  News  የጦርነቱ ጅማሬ ምልክቶች – የአሜሪካ ድጋፍና ኢትዮጵያ ላይ ያለው ጫና
News

የጦርነቱ ጅማሬ ምልክቶች – የአሜሪካ ድጋፍና ኢትዮጵያ ላይ ያለው ጫና

Ethioreview newsEthioreview news—May 31, 20220
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በሺራሮ የሚገኙ የሰብአዊ ድርጅቶች መረጃን ያሰባሰበውንና ሮይተርስ” አየሁት” ያለው የተባበሩት መንግስታት ቡሌቶች የኤርትራ ሃይሎች 23 ዙሮች የተኩስ ጥቃት መፈጸማቸውን ያትታል። ጥቃቱም ጥቂት የተፈናቀሉ ቤተሰቦች የሚኖሩበትን ትምህርት ቤት እንደመታ ይገልጻል። ይህን ጥቃት ሪፖርት ካደረጉት ሰነዶች መካከል አንዱ የ14 ዓመቷ ልጅ መገደሏን፣ በትንሹ 18 ሰዎች መቁሰላቸውንና 12 ቤቶች መጎዳታቸውን አመልክቷል። ይህን ጥቃት ተከትሎ የትህነግ ሃይሎች ባደረጉት መልሶ ማጥቃት ከ300 በላይ የኤርትራ ሰራዊት አባላትና አዛዦች መገደላቸውን መሳሪያም መማረኩን ሮይተርስ አቶ ጌታቸውን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል። እንደ ሮይተርስ ከሆነ የትህነግ ሃይል ሲነካ አጻፋ መልሷል። ለዚህም ምስክሮቹ የዕርዳታ ድርጅቶች ናቸው።

አሜርካ የምስራቅ አፍሪቃ ልዩ መልዕክተኛ አድርጋቸው የነበሩት ፌልትስማን ” ትህነግ በኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ አይወደድም” ሲሉ በመጨረሻው ቃለ ምልልሳቸው ማረጋገጣቸውና እያፈገፈገ ሃይሉን አደራጅቶ ወረራውን በአጭር ቀናት ተቀልብሶ የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ሃይሎች ጦርነቱን በሽንፈት ማጠናቀቃቸው ይታወስል።

“አውቀን ነው ከያዝነው ቦታ የለቀቅነው” በማለት ያስታወቀው የነጻ አውጪው ሃይል ” አሜሪካ ነበር አዲስ አበባ ግቡ ያለችን” ሲል ለሽንፈቱ ምክንያት አቅርቧል። አሜሪካም በውጭ ጉዳይዋ በኩል ” ፈጽሞ አላልኩም” ስትል የላሞኛችሁ ምላሽ ብትሰጥም፣ አቶ ጌታቸው የሴራውን ጥቅልል ውጤት ይፋ ማድረጋቸው ከፌልትስ ማን የመጨረሻ ቃል ጋር በመስማማቱ አቶ ጌታቸው ምን አልባትም በዓመቱ አንድ ትልቅ እውነት መናገራችወና ይኸው ንግግራቸው “በምስክርነት ሰነድ ሊቀመጥላቸው ይገባል” ያሉም ነበሩ።

“ከነ ሙሉ ሃይሌ ወደ ትግራይ ተመልሻለሁ” ያለው ትህነግ አፍታም ሳይቆይ በወጣት ክንፉ አማካይነት ” ከ300 መቶ ሺህ በላይ ወታቶች የት እንደገቡ አይታወቅም” ሲል ማስታወቁ ከትህነግ በኩል የደረሰውን የጉዳት መተን የሚያመላክት፣ በኢትዮጵያም በኩል ሰፊ መስዋዕት መከፈሉ እንደ አገር አሳፋሪ፣ ጥቁር የታሪክ ጠባሳ ሆኗል። ይሁን እንጂ መነሻው ሁሉ በሰሜኑ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ላይ የተፈጸመ የክህደት ጭፍጨፋ በመሆኑ ሙሉ ተጠያቂነቱ የክህደት ቢላውን ባነሳው ወገን ላይ እንደሆነ አብዛኞች ይስማማሉ።

More stories

ለመንግስት ሁሉ አቀፍ የሰላም አሳብ ቀረበለት፤ የእርቅ ኮሚሽን በመጪው ዓመት ህገ መንግስት እስከመቀየር የሚያደርሰውን ስራ ይጀምራል

September 6, 2023

አንድ መቶ አስራ አንድ አገሪቱን በብሄርና በሃይማኖት የሚንጡ ህገወጥ ድረ ገጾች ተለዩ፤ አስሩ ተያዙ

June 1, 2022

ኢትዮጵያ ፌስቡክንና ትዊተርን ሊተካ የሚችል የማህበራዊ ትስስር ገጽ ስራ ላይ ልታውል ነው

August 21, 2021

ኢትዮጵያ አንደ አገር ገናና በነበረችበት ዘመን አሜሪካ አትታወቅም ነበር

October 17, 2022

አቶ ኦባንግ ከሚመሩት ለሰብአዊ መብት ተቆርቋሪ እንደሆነ የሚነገርለት የአዲስቲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ solidarity movement for a new ethiopia (SMNE) ይህ ጽሁፍ እስከታተመበት ቀን ድረስ በኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ የተፈጸመውን የክህደት ግፍ በዝምታ ያለፈና፣ ዝም ለማለቱ በቂ ምክንያት ያላቀረበ፣ በወጉም በሚዲያ ያላስታውቀና ያልተጠየቀ መሆኑንን በመገረም የሚያወሱ፣ የትህነግ ሃይሎች በመከላከያ ላይ የፈጸሙትን የክህደት ወንጀል ከኢትዮጵያ በተቃራኒ የቆሙና ውገናቸውን በገሃድ ያሳዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትና ሚዲያዎች ሳይቀሩ ያመኑት ጉዳይ ነው። በዚህም መነሻ ለጦርነቱ መነሳት ትህነግ ምክንያት ስለመሆኑ መከራከሪያ አይቀርብም።

በዚህ የጭንቅ ቀን ነው ኤርትራ ከክህደት እርምጃው ተርፎና በሃይሉ ከበባውን ሰብሮ ወደ ኤርትራ ምድር የዘለቀውን የኢትዮጵያ መከላከያ በማልበስ፣ በማብላት፣ በማጠጣትና ከለላ በመሆን ታላቅ ውለታ የፈጸመችው። የኤርትራ የውቅቱ በጎ ተግባርና ምላሽ ” ከኤርትራ ጋር ወዳጅ ባንሆን ኖሮ ምን ይውጠን ነበር” በሚል በገሃድ መንግስትና ሕዝብ የአክብሮት ምላሽ ሰጥተዋል።

ከዳግም ወረራው መቀልበስ በሁዋላ አፋርን ድጋሚ ይዞ የነበረው ትህነግ የኢትዮጵያን መንግስት የተናተል የተኩስ አቁም እርምጃ ባለማክበር ቢከሰስም ” እርዳታ በደንብ ከገባልኝ ለቅቄ እወጣለሁ” ሲል ቆይቶ አፋርን ለቆ መውታቱን አስታውቋል። አሁንም ግን አንዳንድ ቦታዎች ላይ እንዳለ ይነገራል።

በከፈተኛ መጠን በአየርን በየብስ እርድታ እየገባለት ያለው የትግራይ ክልል ላለፉት ሶስት ሳምንታት ፊቱን ወደ ኤርትራ አዙሯል። ኤርትራ በገሃድ የሩሲያ ደጋፊ መሆኗን፣ የቀይ ባህርንም ለሩሲያ የጦር ኮሪዶርነት መፍቀዷ ያላስደሰታት አሜሪካ ከቀድሞ ጀምሮ በፕሬዚዳንት ኢሳያስ ላይ ካላት ጥላቻ ጋር ተዳምሮ ትህነግ ልዩ የቤት ስራ እንደተሰጠው፣ ለዚህም የሎጂስቲክ ችግር እንዳይገጥመው እርዳታ እንዲጎርፍለት መደረጉን አንዳን ወገኖች እየተናገሩ ባለበት ወቅት ነው የጦርነቱ ወሬ ገሃድ የሆነው።

የትህነግ ልሳን የሆኑት አቶ ጌታቸው ይፋ እንዳደረጉት በትህነግ ሃይሎችና በኤርትራ መካከል ጦርነት ተካሂዷል። ጦርነቱ መካሄዱን ኢትዮጵያም እንደምታውቅ አረጋግጣለች። ኤርትራ ግን ለጊዜው ያለችው ነገር የለም። አቶ ጌታቸው በትዊተር ገጻቸው የጦርነቱን መካሄድ ሳይሆን ያጎሉት ጉዳይ “የኤርትራ ኃይሎች ቀጠናውን ወደማያባራ ግጭት እየወሰዱት ነው” የሚለውና ትህነግን ከተዘነጋበት የምስራቅ አፍሪቃ አጀንዳ የመክተት ነው። ይህን ሲያተነክሩ “ይህም ወደ ሰላም ሊደረግ የሚችል ጉዞን የሚያሰናክል ነው” በማለት የቀጠናው የሰላም ጠንቅ የኤርትራ መንግስት እንደሆነ ገልጸዋል።

ወረራው ከተቀለበሰ በሁዋላ ” ከማን ጋር ነው የምንደራደረው? ጦርነቱ በሳምንታት ያልቃል” ባሉበት ሚዲያ ሌተና ጀኤነራል ጻድቃን ” የኤርትራን መንግስት እንዲነቀል ድጋፍ ሊደረግ የገባል” ሲሉ ካሰራጩትና ዶክተር ደብረጽዮን ” አግዙን፣ ኤርትራ ውስጥ ያለው መንግስት መወገድ አለበት” ሲሉ ጥሪ ባቀረቡበት ወቅት ዋና ምክንያት የሆነው ” ሻዕቢያ የአፍሪቃ ቀንድ ስጋት ነው” የሚለው ጉዳይ ነው።

“የትግራይ መከላከያ ሃይል” ተብሎ የተሰየመውን ሰራዊት በማግዘፍና በቀጣናው የአሜሪካናን የአውሮፓን ጥቅም የሚያስከበር ልዩ አቅም እንዳለው ተደርጎ በተለያዩ ወገኖች ሲቀርብ የነበረውን ቅስቀሳ ” አስተማማኝ ሃይል ስትገነባ ትከበራለህ” በሚል የፖለቲካ ሚዛን ደጋግመው የሚናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ዛሬ ላይ በኢትዮጵያ የተገነባው ከደርግ ውድቀት በሁዋላ በምሁራን፣ በዲሲፒሊን፣ በኢትዮጵያዊነትና እጅግ በዘመነ መሳሪያ የደረጀ መሆኑ እየተመሰከረ ነው። ለዚህም ይመስላል ትህነግ እጀምረዋለሁ የሚለውን ጦርነት ያልገፋበት የሚል ጉዳይም እየተነሳ ነው።

በኤርትራ በኩል ጦርነቱ ከተጀመረ እስከ ቀብር ድረስ እንደሚሄድ ኢሳያስ ማስተንቀቃቸውን ኤርትራ ፕሬስ አመልክቷል። የኤርትራ ፕሬስ ከሶስት ሳምንት በፊት እንዳለው ኤርትራን ለማጥቃት ከታሰበ የትህነግን ሃይል የመደምሰስ አቅም ኤርትራ በተጠንቀቅ ማቆሟን አመልክቷል። ይህ በተባለ አጭር ጊዜ የትህነግ ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳ ቅዳሜና ዕሁድ የኤርትራ ሠራዊት በሽራሮ በኩል ጥቃት ከፍቶ እንደነበር አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ተንኳሹ የትህነግ ሃይል እንደሆነና በውጤቱም ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት አታውቋል። ኤርትራ ዝምታን መርጣለች።


[jetpack_subscription_form show_subscribers_total=”false” button_on_newline=”false” custom_font_size=”16px” custom_border_radius=”16″ custom_border_weight=”5″ custom_padding=”14″ custom_spacing=”10″ submit_button_classes=”has-vivid-red-border-color” email_field_classes=”has-vivid-red-border-color” show_only_email_and_button=”true” success_message=”Success! An email was just sent to confirm your subscription. Please find the email now and click ‘Confirm Follow’ to start subscribing.”]

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ንለገሰ ቱሉን ጠቅሶ ለአል ዐይን አማርኛ እንደጻፈው ትህነግ የኤርትራ ጦር ጥቃት ከፈተ በሚል የሚያሰራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ ነው። አቶ ጌታቸው ግን ከቅዳሜና እሁድ ተከስቷል ካሉት ግጭት በተጨማሪ ግንቦት 16 ቀን 2014 ዓ. ም የኤርትራ 57ኛ እና 21ኛ ክፍለ ጦሮች ወደ ትግራይ ክልል በመዝለቅ ጥቃት መሰንዘሩን አስታውቀዋል።

አዲአዋላ አካባቢ በነበረ ውጊያ የህወሃት ታጣቂዎች ጥቃቱን እንደመከቱ ፣ የትህነግ ኃይሎች መልሶ ማጥቃት መፈጸማቸውንና የኤርትራ ወታደሮች  መገደላቸውና መቁሰላቸውን እንዲሁም “በርካታ” ያሏቸው የጦር መሣሪያዎችን መማረክ እንደቻሉ ገልጸዋል። ይሁን እንጂ ይህ በነጻና ገለልተኛ ሃይል አልተረጋገጠም።

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ለቢቢሲ በሰጡት ምላሽ በአሁኑ ጊዜ “በኤርትራ በኩል ጦርነት ይከፈታል የሚል እምነት የለንም” ብለዋል። ጨምረውም የህወሓት ኃይሎች ለጦርነት እየተዘጋጁ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ለአል-ዐይን ሲናገሩ ግን ትንኮሳ ያደረገው ህወሃት እንደሆነና የተመቱትም ራሳቸው የህወሃት ታጣቂዎች መሆናቸውን ነው ያስታወቁት። ሚኒስትሩ በኤርትራና በህወሃት መካከል ግጭት እንዲፈጠር ያደረገው ህወሃት መሆኑን ገልጸው በዚህ ሁኔታ ህወሃቶች “ሬሳ እንኳን ማንሳት አልቻሉም፤ በጣም ብዙ ሰው ወድሞባቸዋል” ብለዋል።

ሚያዚያ 30 ቀን 2014 ዓ.ም የትግራይ ኃይሎች ከኤርትራ ጋር አዋሳኝ በሆኑት የራማና ባድመ አካባቢዎች ጦርነት አካሂደው እንደነበር ስለ ጉዳዩ የሚያውቁ ክፍሎችን ጠቅሰን መዘገባችን ይታወሳል። ጥቃቱ በራማና ባድመ አካባቢ ባለው የኤርትራ ጦር ላይ የተሰነዘረ ሲሆን፣ አስቀድሞ መረጃ የደረሳቸው የኤርትራ ሃይሎች ሆን ብለው በማፈግፈግ ቀለበት ውስጥ ከተው በትህነግ ሃይሎች ላይ ጉዳት ማድረሳቸው በወቅቱ ተዘግቧል። የትህነግ ወገኖች ግን ጥቃቱ ከኤርትራ ወገን መሆኑንን አመልከተው ኪሳራ ማድረሳቸውን ገልጸውም ነበር።

ይህን የጦርነት ግጭት ኢትዮጵያ ትግራይ አካሏ በመሆኗ እንዴት ልታየው ነው? ሚናዋስ ምን ሊሆን ይችላል? የሚሉ ሰፊ መነጋገሪያ ጉዳዮች ቢኖሩም ለአል አይን ይህን አሳብ አስመክቶ ዶክተር ለገሰ ፣ህወሃት ትንኮሰውን የሚፈፅመው ሁለቱን ሀገራት ወደ ግጭት ለማስገባት እንደሆነ ጠቅሰው፣ “ኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ምንም ቢሆን ልዩነት አይፈጠርም። አይሳካም” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

የትህነግ ሰራዊት በአሜሪካ የአየር ላይ ምልከታ ” ጂፒኤስ” እገዛ ይደረግለት እንደነበር፣ በዚህም የኢትዮጵያ ሃይሎች አሰላለፍ፣ ብዛት፣ አቅጣጫ፣ የከባድ መሳሪያ አሰላለፍ በምስልና በሂሳብ እየተሰላ ይደርሰው እንደነበር በወቅቱ ይፋ ያደረጉ ወገኖች እንደሚሉት አሁንም ትህነግ ይህን ድጋፍ በማግኘት ኤርትራን ለማጥቃት መነሳቱን እየገለጹ ነው።

በፕሬዚዳንት ኢሳያስ ላይ ጥርሷን የነከሰችው አሜሪካ በሶማሌ መንግስት እንዲለውጥ ብታደርግም ሕዝብ ደስተኛ እንዳልሆነ የጀርመን ድምጽ እንግሊዘኛ ክፈለጊዜ የሞቃዲሾ ዘጋቢ ማመልከቱ የሚጠቁሙ ” አሜሪካ በሶማሌ እንዳደረገችው ኤርትራ ማድረግ አትችልም። የኤርትራ ህዝብም እሺ አይልም። ስለዚህ አሁን ያለው አማራጭ ትህነግን በማገዝ በወታደራዊ ሃይል ኢሳያስን ለማስወገድ መሞከር ነው” እነዚህ ክፍሎች ትህነግ ከአሜሪካ ሙሉ ድጋፍና እውቅና እንደተሰጠው ያምናሉ። ይህ ባይሆን ከቶውንም ትህነግ በራሱ አቅም ወደዚህ ጦርነት ለመግባት አይወስንም። አሁን ጥያቄ የሆነው የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አቋም ነው።

በተለያዩ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ጫና የኢትዮጵያን መንግስት አንቃና አስገድዳ የያዘቸው አሜሪካ በመደረደሪያዋ ላይ ለጊዜው ያስቀመጠችውን ኤች አር 6600ን ጨምሮ ለዚህ ተግባር ለትተቀም እንደምትችል ይገመታል። ወደ ወልቃይትና አፋር “ከበባ ለመስበር” በሚል ሰፊ ዋጋ የከፈለው ትህነግ ከኤርትራ ጋር ሙሉ ውጊያ ከገባ ኢትዮጵያ በአሜሪካ ማስፈራሪያ ተቀፍድዳ ተመልካች ትሆና ይሆን?

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ሃላፊ ሚኒስትሩ ” ተንኳሹ ትህነግ ነው። አላማውም ኢትዮጵያና ኤርትራን ለማጋጨት ነው” ሲሉ የገለጹበት አግባብ ለጊዜው ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር ምንም አይነት ነፋስ እንዲነፍስ አለመፈለጓን የሚያሳይ መስሏል። እንደውም የኢትዮጵያ መከላከያ በተጠንቀቅ በያለበት ልምምዱን እያደረገ እንዲቆይ መታዘዙ፣ መንግስትም ሆነ የሰራዊቱ አመራሮች በአጭር ጊዜና አነስተኛ መስዋዕት ጠላትን በማያዳግም አኳኋን መምታት የሚችልበት አቋም ላይ እንደሚገኝ ማስታወቃቸው ትርጉሙ ሌላ እንደሆነ የሚገልጹም አሉ።

በቅርብ ጊዜያት ብቻ በርዳታ ስም ወደ መቀለ ሲደረጉ የነበሩ በረራዎች ለትህነግ ሃይሎች በትከሻ ላይ የሚያዘውን የአየርና የታንክ ማቃጠያ መሳሪያ አቀብለው ይሆን? የሚለው ጥያቄ የበርካቶች ነው። ይህ አሜሪካ ሰራሽ በትከሻ የሚያዝ ቀላል ግን ዘመናዊ ጸረ አውሮፕላንና ታንክ፣ በዩክሬን ጦርነት ሩሲያን ያስቸገረ እንደሆነ እየተነገረለት ነው። ቀደም ሲል ” መቋቋም ያልቻልነው የድሮን ጥቃት ነው” ሲሉ የትህነግ አመራሮች ማስታወቃቸው ይታወሳል። እናም ስንቅ በብዛት እየገባለት ያለው የትህነግ ሃይል ይህን መሳሪያ አግኝቶ ከሆነ፣ በጂፒኤስ ከተረዳ ለኤርትራ ፈተና እንዳይሆን የሚል ስጋት አለ። ትህነግ ወደ አማራ ክልልና አፋር በእግረኛ ሃይሉ ዳግም ቢመጣ ህዝብ በጥፍሩም ሆነ በጥርሱ ስለሚዋደቅ እንደማይሞክረው የሚገልጹ ኢሳያስና አብይ አህመድ ለዚህ መላ ማፈላለግ ሊከብዳቸው እንደማይችል፣ ሩሲያም ኤርትራን በመሳሪያ ማደርጀቷ ሌላው ስጋቱ ከስጋት በላይ እንዳይሄድ የሚያደርግ እንደሆነ የሚጠቁሙም አሉ።

ትህነግ በራሱ መሪዎች ሊሰጥ፣ ሲሰጥ ይጋብኝ እንደማይጠይቅ አምኖ በፈረመው መሰረት የባድመን ጉዳይ በመቋጨት ለትግራይም፣ ለኤርትራም፣ ለተቀረው የኢትዮጵያ ክፍል ሰላም እንዲሰፍን ትልቁን ድርሻ ሊወጣ እንደሚችል፣ ከጊዜ በሁዋላ ህዝብ ድነበሩን አፍርሶ እንድነበረው እንደሚኖር ልምዳቸውን ገልጸው የሚናገሩ አሉ።



  • President Taye champions Africa’s dev’t and regional transformation with GERD at UNGA 80
    In a comprehensive address to the 80th session of the United Nations General Assembly in New York, President Taye Atske-Selassie of Ethiopia underscored Africa’s development achievements, called for urgent global action to tackle the continent’s debt crisis, and highlighted the transformative impact of the Grand Ethiopian… Read more: President Taye champions Africa’s dev’t and regional transformation with GERD at UNGA 80
  • Two African countries refuse to recognise Palestine. Here’s why
    At the United Nations General Assembly this week, one country after another rose to declare its recognition of a Palestinian state. Britain, Canada, Australia, France and Malta joined the growing chorus, bringing the total number of UN member states extending recognition to 157 – more than… Read more: Two African countries refuse to recognise Palestine. Here’s why
  • UN Chief Stresses Need for Countries to Adopt Climate-smart Food Policies to Reduce Reliance on Food Imports
    UN Secretary-General Antonio Guterres stressed the need for countries to adopt climate-smart food policies and enhance private sector participation to reduce reliance on food imports. The second UN Food Systems Summit is taking place in Ethiopia’s capital Addis Ababa in the presence of several heads of… Read more: UN Chief Stresses Need for Countries to Adopt Climate-smart Food Policies to Reduce Reliance on Food Imports
  • Puntland Intercepts Cargo Ship Carrying Weapons To Mogadishu
    ByMI News Network Authorities in Somalia’s semi-autonomous Puntland region have intercepted a cargo vessel which was carrying a massive consignment of military vehicles and weapons to Mogadishu. The vessel, per reports, is of foreign origin and was confiscated close to the coastal area of Bareeda in… Read more: Puntland Intercepts Cargo Ship Carrying Weapons To Mogadishu
NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

Ethioreview news

A journalist

ከ370 ቢሊዮን ብር በላይ በባንኮች ላይ የማጭበርበር ወንጀል ሙከራ ተደርጓ ከሽፏል፣1.8 ቢልዮን ተዘርፏል
Eritrean refugee women face sexual violence in tigray
Related posts
  • Related posts
  • More from author
ART and CULTURE

አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱ

May 17, 20260
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 20260
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 20260
Load more
Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Read also
ART and CULTURE

አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱ

May 17, 20260
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 20260
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 20260
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 20260
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 20260
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 20260
Load more
Recent Posts
  • አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱ May 17, 2026
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE - VOICES OF ETHIOPIA
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedbusinesshotarchivetips
    © Copyright 2026, All Rights Reserved
    • CONTACT
    • INTERVIEW
    • law
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • ያበደው
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2
    • Home Demo news