Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  አፍሪካ የፓን አፍሪካኒዝምን የወጣት መሪዎች ጉባኤ እንዲኖራት ኢትዮጵያ አሳብ አቀረበች፤ የፓን አፍሪካኒዝም ፎረምን ሊያካሂድ ሊካሄድ ነው
News

አፍሪካ የፓን አፍሪካኒዝምን የወጣት መሪዎች ጉባኤ እንዲኖራት ኢትዮጵያ አሳብ አቀረበች፤ የፓን አፍሪካኒዝም ፎረምን ሊያካሂድ ሊካሄድ ነው

Ethioreview newsEthioreview news—February 15, 2023
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 8/2015 የአፍሪካ ኅብረት ፓን አፍሪካኒዝምን ማጠናከር የሚያስችል የወጣት መሪዎች ጉባኤ ሊኖረው ይገባል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ገለጹ። የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የፓን አፍሪካኒዝም ፎረምን ሊያካሂድ እንደሆነ ተገለጸ።

ኢትዮጵያ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ በነበረችበት አጋጣሚ በብዙ መድረኮች ከጎኗ በመቆም አጋርነታቸውን ላሳዩ አፍሪካዊያንም ምስጋና አቅርበዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፤ ዛሬ በተጀመረው 42ኛው የአፍሪካ ኅብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ ላይ በመገኘት ንግግር አድርገዋል።

በንግግራቸውም የአፍሪካ አገራትና የአፍሪካ ኅብረት እንዲሁም አጋር አካላት በኢትዮጵያ በዘላቂነት ግጭት ለማቆም ለተደረሰው ሥምምነት ላደረጉት ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።

More stories

“ዛሬ እኛ ነን ነገ ደግሞ እናንተ ትሆናላችሁ” ቀዳማዊ ኀይለ ሥላሤ

May 5, 2023

ሰላም፣እርጋታና የዜጎች ደህንነት ለኢትዮጵያውያን ፍትሃዊ እድገት ወሳኝ ናቸው – በአሜሪካ የህዝብ ዲፕሎማሲ አማካሪ ምክር ቤት

May 17, 2021

ትግራይ በራሷ ልጅ አንደበት ምስክርነት

June 28, 2021

“ኑ ! የወልቃይት ምድር ነጻ ወጥቷል” በስደት የሽሽት ኑሮ ላይ የነበሩ አማሮች ወደ ወልቃይት ጠገዴን ሰቲት ሁመራ ተመለሱ

June 17, 2021

በተለይም ደግሞ አንዳንድ አካላት በኢትዮጵያ ላይ ጫና ሲያሳድሩ በባለብዙ ወገን መድረኮች ላይ ጭምር አፍሪካዊያን ከኢትዮጵያ ጋር በመሰለፍ አጋርነታቸውን ማሳየታቸውን አስታውሰዋል።

ኢትዮጵያ ባሳለፈቻቸው የፈተና ጊዜያት ከአፍሪካ ኅብረትና ከአፍሪካዊያን ያገኘነው ድጋፍ አኩርቶናል፤ በአፍሪካ ላይ ያለንን እምነትም እጅጉን አጠናክሮታል ብለዋል።

በተለይም ለአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፋቂ ማኅማት፣ ለቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሊሴንጎ ኦባሳንጆ እንዲሁም ለቀድሞ ኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ምስጋና አቅርበዋል።

በመንግሥትና በሕወሓት መካከል የተደረሰው የሠላም ሥምምነት “ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ መስጠት የሚለውን የኅብረቱ ቁልፍ መርህ ገቢራዊ በማድረግ ትልቅ ማሳያ ነው ሲሉም ተናግረዋል።

የሠላም ሥምምነቱ አሁን ላይ በተለያዩ የትግበራ ደረጃ ላይ መሆኑን ጠቁመው የሰብዓዊ ድጋፍ በማቅረብ በግጭቱ የተቋረጡ አገልግሎቶችን መልሶ በማስጀመር አመርቂ ውጤቶች መገኘታቸውን ጠቅሰዋል።

ጎን ለጎንም ከአፍሪካ ኅብረት ጋር በመሆን የሠላም ሂደቱ የአፈጻጸም ትግበራ በመልካም ደረጃ ላይ መሆኑን ገልጸው በተለይም ትጥቅ በመፍታትና ወደ ማኅበረሰቡ በመቀላቀል አበረታች ውጤት እየተገኘ ነው ብለዋል።

ከዚህ ጎን ለጎን ኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ከመንግሥታቱ ድርጅት የሰብዓዊ መብት ተቋም ጋር በጋራ ያደረጉትን ጥናት ተከትሎ ያቀረቡትን ምክረ-ሃሳብ በመቀበል እየተገበረች ነው ብለዋል።

በተለይም ደግሞ ተጠያቂነትን ለማስፈን የሚኒስትሮች የጋራ ግብረ-ሃይል በማቋቋም እየሰራች መሆኑን ገልጸው እንዲያም ሆኖ የተ.መ.ድ የሰብዓዊ ተቋም ይህንን የኢትዮጵያ ጥረት ወደ ጎን ማለቱ ተቀባይነት እንደሌለው ነው ያስረዱት።

የአፍሪካ የሰብዓዊና የሰዎች መብት ኮሚሽን በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለማጣራት የተናጠል ቡድን ማቋቋሙ ኢትዮጵያ የተመድ አቻ ተቋም ጋር በመሆን የምታካሂደውን ጥረት የሚያቃልል ነውም ብለዋል።

ያም ብቻ ሳይሆን በጋራ ጥናት ይካሄድ የሚለውን የኢትዮጵያን ጥያቄ ውድቅ ያደረገ መሆኑን ጠቁመው በሠላም ሥምምነቱ መሰረት ኢትዮጵያ በሽግግር ፍትህ ላይ ብሔራዊ ምክክር እያደረገች ያለውን ጥረትም ያላገናዘበ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በመሆኑም አፍሪካዊያን አስካሁን የሚያደርጉትን አጋርነት አሁንም በድጋሚ እንዲያሳዩ ጠይቀዋል።

ያለፉት ሁለት ዓመታት በርካታ ቁም ነገሮችን ተምረናል ያሉት አቶ ደመቀ ሰላም ለማረጋገጥ ውስጣዊ ጉዳዮችን በራስ መምራትና በወጣቶች የፓን አፍሪካኒዝም ጽንሰ ሃሳብ ማስረጽ ያስፈልጋል ብለዋል።

ኢትዮጵያ ፓን አፍሪካኒዝም ለአፍሪካ አንድነትና ምጣኔ ሃብታዊ አድገት ወሳኝ ነው ብላ ታምናለች ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፤ በተለይም በአፍሪካ የጥይት ድምጽ እንዳይሰማ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት አፍሪካዊያን በባለቤትነት መምራት አለባቸው ብለዋል።

በተለይም የአፍሪካ ኅብረት የሰላምና የደህነነት የፖለሲ ማዕቀፎችን በአግባቡ በመጠቀም በአህጉሪቱ የሚከሰቱ የጸጥታ ችግሮች ዘላቂ እልባት መስጠት ይገባል ብለዋል።

ይህንን ከግምት በማስገባት ኢትዮጵያ ባሳለፍነው የፈረንጆች ዓመት ከተለያዩ የአፍሪካ አገራት የተውጣጡ ወጣቶች በፓን አፍሪካኒዝም እሳቤዎች ላይ እንዲመክሩ ማድረጓን ገልጸዋል።

በመሆኑም የአፍሪካ ኅብረት በአህጉሪቱ ፓን አፍሪከኒዝምን ለማጠናከር የሚያስችል ዓመታዊ የወጣት መሪዎች ጉባኤ ማስተናገድ አለባት በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ይህም የወደፊት የአፍሪካ ኅብረት ሥራዎችን ከወጣቶች ጋር ለማሰናሰልና የፓን አፍሪካኒዝም መርሆዎችን ለማስቀጠል ያስችላል ብለዋል። ወጣቶች የሚሰሯቸው ሥራዎች በአፍሪካ ኅብረት ጥላ ስር እንዲካሄድና የአፍሪካ አንድነት እንዲሁም ምጣኔ ሃብታዊ አድገት እንዲኖር ያስችላል ነው ያሉት።

የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የፓን አፍሪካኒዝም ፎረምን ሊያካሂድ ነው

የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የመጀመሪያ የሆነውን የፓን አፍሪካኒዝም ፎረም ሊያካሂድ ነው። የተቋሙ ርዕሰ አካዳሚ ዶክተር ምህረት ደበበ እና ምክትሎቻቸው ይህንኑ ሁነት በማስመልከት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የመጀመሪያ የሆነውን ፎረም የፊታችን እሁድ ለማካሄድ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።

የፎረሙ ዋነኛ ዓላማ የፓን አፍሪካኒዝምን ንቅናቄ ዳግም ለማነቃቃት ያለመ መሆኑ የገለጹት ዶክተር ምህረት ዘመናዊ የቀኝ አገዛዝ እሳቤን መታገልና የአፍሪካን ሁለንተናዊ ለውጥ ለማሳካት ያግዛል ብለዋል። በፎረሙ የአረንጓዴ አሻራ ልምድና ተሞክሮ የሚቀርብ ስለመሆኑም ጠቅሰዋል።

የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ከኢትዮጵያ አልፎ ለአሕጉሪቷ ሕዝቦች የእውቀት ማእከል ለመሆን እየሰራ መሆኑን የገለጹት ዶክተር ምህረት የአሁኑ ፎረም መዘጋጀትም የዚሁ ማሳያ ነው ብለዋል። በፎረም ላይ በርካታ የአፍሪካ አገራት መሪዎች፣ የአህጉሪቱ ምሁራንን ጨምሮ ከ300 በላይ ተሳታፊዎች እንደሚኖሩ ይጠበቃል። የፓን አፍሪካኒዝም ፎረምን ከአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን በየዓመቱ የማካሄድ ዕቅድ እንዳለም ታውቋል።

ዜናው የኢዜአ ነው

POLITICS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
አፍሪካ በጤናና በምግብ ያለባትን ቸግር በዘላቂነት ለመፍታት
AU-Led Peace Process Demonstrates True Meaning Of “African Solution To African Problems”
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2