ሀገር ፈተና ውስጥ ሳለች ብርቱ ክንዶቻቸውን ጋሻ አድርገው ሀገር እና ሕዝብን ከውርደት ታድገዋል፡፡ እንደ አባቶቻቸው ክተት ሲባሉ ከትተው ግንባራቸውን ለአሩር፣ ደረታቸውን ለጦር እግሮቻቸውን ለጠጠር ሰጥተው ታሪክ እና ሀገርን አስጠብቀው አቆይተዋል፡፡ ታሪክ የማይረሳ እና ትውልድ በየዘመኑ የሚያስታውሰው ጀብዱ የሰሩት የዘመኑ አናብስት የቀድሞው የአማራ ልዩ ኃይል አባላት፡፡
የክልል ልዩ ኃይል አባላትን በላቀ ደረጃ መልሶ ማደራጅት እንደሚያስፈልግ ታምኖበት ወደ ሥራ ከተገባ ሳምንታት ተቆጥረዋል፡፡ ምንም እንኳን ይላሉ የልዩ ኃይል አባላቱ “ጦሩን በላቀ ደረጃ መልሶ ለማደራጀት የተሰጠው ጊዜ አጭር በመኾኑ በቂ ውይይት አለመደረጉ ተፈጥሮ ለነበረው አለመግባባት ምክንያት ቢኾንም፤ በቀጣይ የክልሉ መንግሥት እና ሕዝብ የሚሰጠንን ማንኛውም ግዳጅ በላቀ ብቃት ለመፈጸም የሚያስችል ዝግጅት እያደረግን ነው” ብለዋል፡፡
የልዩ ኃይል አባላቱ በፌዴራል እና በክልል የጸጥታ ተቋማት ውስጥ እንደየፍላጎታቸው እና ምርጫቸው እንዲሰማሩ አሠራር ተዘርግቶ እየተተገበረ ነው፡፡ ከቀረበላቸው ምርጫዎች መካከል የአማራ ክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽንን ከመረጡት ኮሚሽኑ የሚሰጠውን የተሃድሶ ሥልጠና ከሚወስዱ አባላት መካከል ረዳት ኢንስቴክተር ከፍያለው ደጀንን እና ሃና ደገፉን አሚኮ አነጋግሯቸዋል፡፡
ባለፉት ዓመታት ክልሉ እና ሀገሪቱ ከነበሩበት የህልውና ሥጋት አንጻር በተለያዩ ግንባሮች የአማራ ሕዝብ እና መንግሥት የሰጡንን አደራ በብቃት ለመወጣት ሞክረናል ያለን የነብሮ ክፍለ ጦር የሕግ ክፍል ኃላፊ የነበረው ረዳት ኢንስፔክተር ከፍያለው ደጀን በቀጣይም የክልሉ ሕዝብ እና መንግሥት የሰጡኝን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት ጥረት አደርጋለሁ ብሏል፡፡ ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ከሌሎች የጸጥታ ተቋማት የተለየ የራሱ ተግባር እና ኃላፊነት አለው ያለን ረዳት ኢንስፔክተር ከፍያለው የኮሚሽኑን አሠራር ለመገንዘብ የሚያስችል የተሃድሶ ስልጠና መውሰዳችን ተገቢ ነው ብሏል፡፡
በአማራ ልዩ ኃይል የነበልባል ክፍለ ጦር አባል የነበረችው ሃና ደገፉ ከቀረቡላቸው አማራጮች መካከል የማረሚያ ቤት ኮሚሽንን መምረጧን ገልጻ በቀጣይም የተሰጣትን ተግባር እና ኅላፊነት በብቃት ለመወጣት መዘጋጀቷን ገልጻለች፡፡
የአማራ ልዩ ኃይል በቆይታው የክልሉን ሕዝብ በላቀ ብቃት አገልግሏል ያሉት አባላቱ የተሰው እና ጉዳት የደረሰባቸውን የሠራዊቱን አባላት እና ቤተሰቦች በዘላቂነት ማቋቋም የክልሉ መንግሥት ኃላፊነት ሊኾን ይገባል ብለዋል፡፡ ሀገር እና ሕዝብ በፈለገቻቸው ጊዜ በየትኛውም ግዳጅ ለመሳተፍ ዝግጁ እንደኾኑም ተናግረዋል፡፡
የክልሉን ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ምርጫቸው ያደረጉ የልዩ ኃይል አባላት ኮሚሽኑ የነበሩበትን ክፍተት ለመሙላት ጉልበት ይኾናሉ ያሉን ደግሞ የአማራ ክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ውቤ ወንዴ ናቸው፡፡ የክልሉ ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ከሌሎች የጸጥታ ተቋማት በተለየ የሕግ ታራሚዎችን የማረም፣ የማነጽ፣ የማጀብ እና የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት ያሉት ረዳት ኮሚሽነር ውቤ ለዚህ ተልእኮ ብቁ የሚያደርግ ተጨማሪ የተሃድሶ ሥልጠና መሥጠት አስፈላጊ ነበር ብለዋል፡፡
በአዲስ ኮሚሽኑን የተቀላቀሉ የልዩ ኃይል አባላት ክብራቸውን፣ ጥቅማቸውን እና ደረጃቸውን የሚመጥን ስምሪት ይሰጣቸዋል ያሉት ምክትል ኮሚሽነሩ የነበራቸውን ወታደራዊ ልምድ፣ እውቀት፣ ሥነ-ምግባር እና ክህሎት በመጠቀም የኮሚሽኑን አፈጻጸም ወደ ላቀ ደረጃ ያደርሳሉ የሚል እምነት እንዳላቸውም ገልጸዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ታዘብ አራጋው አሚኮ
- አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱበዙፋን ኡርጋ ደራሲነት የተጻፈውን ሌንጮ ለታ ትግል ሕይወቱ መጽሐፍን አነበብኩት። መጽሐፉ በ471 ገጾች እና በሦስት ክፍሎች ተቀንብቧል። የመጀመሪያው ክፍል ከልጅነት እስከ ትግል… Read more: አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱ
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም።… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው







