Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  law  General  ብሔራዊ ጥቅምን በአግባቡ እና በጥንቃቄ መያዝ ያስፈልጋል!!
GeneralPOLITICS

ብሔራዊ ጥቅምን በአግባቡ እና በጥንቃቄ መያዝ ያስፈልጋል!!

Ethioreview newsEthioreview news—January 19, 2024
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ሀገራችን ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚ በተፈጸመ ከፍተኛ የሆነ ስህተት ወይም የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ በሰጠ ገዢ መንግሥት ምክንያት ከ 1985 ዓ.ም ወዲህ ባለው ጊዜ ጥቂት ከሚባሉ የባህር በር ከሌላቸው ሀገራት መሀከል አንዷ እንድትሆን ሆኗል። በመሆኑም ይህ ክስተት በቀንዱ እንደ ኢትዮጵያ ያለች በህዝብ ቁጥር እና በኢኮኖሚው ግዙፍ የሆነች ሀገር ላይ በኢኮኖሚው ረገድ ከፍተኛ ተጽዕኖ ውስጥ ሲከታት በገሀድ እንደሚታየው ከኢኮኖሚያዊ ጥቅም ባሻገር የጸጥታ እና ደኅንነትም ላይ የሚያመጣው ተጽዕኖ ከፍተኛ እየሆነ መጥቷል።

ሀገራችን ከላይ በተጠቀሰው መልኩ የባህር በሯን ያጣች ቢሆንም የተባበሩት መንግሥታት የባህር ህግ ሥምምነት አንቀጽ 125 በግልጽ እንደሚያስቀምጠው ባህር በር አልባ የሆኑ ሀገራት በሥምምነቱ የተጠቀሱ መብቶችን ለመጠቀም የባህር በር የመጠቀም መብት እንዳላቸው ይህም ትራንዚቱን የምትሰጠውን ሃገር ህጋዊ ጥቅም ባልነካ እና ከዚችው ሃገር ጋር በሚደረግ ሥምምነት የሚደረግ እንደሆነ ይደነግጋል። የሃገራችን መንግሥት ባለፉት ጥቂት ወራት ይህን መብት ለመጠቀም እንደሚፈልግ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስተር በተደጋጋሚ ሲናገሩ የተሰማ ሲሆን በቅርብ ቀን ይህንን ለማድረግ የሚያስችል የመግባቢያ ሰንድ (MoU) ከሶማሊላንድ ጋር መፈራረሙንም አሳውቋል።

የዚህን ሥምምነት በተለየ ሁኔታ እንዲታይ ያደረገው በተባበሩት መንግሥታት አባል ሀገራት ለሶማሊላንድ በይፋ ይህ ነው የሚባል ዕውቅና አለመስጠታቸው ሲሆን ነገር ግን ይህቺ እንደ አውሮፓውያኑ ዘመን አቆጣጠር 1991 ዓ.ም. ጀምሮ የካይሮን ሥምምነት መሰረት አድርጋ እራሷን ሀገር ብላ ባወጀች ሀገር፤ የአፍሪካ ሕብረት እውነት አፈላላጊ ልዑክ (fact finding mission) እንደ አውሮፓውያኑ ዘመን አቆጣጠር በ 2005 ዓ.ም ባደረገው ምልከታ ሃገሪቱ ከብሪታንያ ቅኝ ግዛት ስትወጣ የወረሰችው ዳር ድንበር (territory) ይዛ ያለች መሆኑን፣ ነጻነቷን ካወጀች በኋላ ባሉት ጊዜያት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመተግበር የሚያስችሉ መሰረት የጣለች መሆኑ እና የዘመናዊ ሃገር መገለጫዎች የሆኑ ህገመንግሥት እና መሰል ጉዳዮች እንዳሏት እና ሌሎች ዝርዝሮችን አስቀምጦ ለህብረቱ “ከ 1990 በፊት ከሶማሊ ሪፑብሊክ ጋር የተደረገው ህብረት (union) አለመጽደቁን እና ህብረቱ ተፈጽሞ እስኪያበቃ ውጤታማ አለመሆኑን (malfunctioned) ጠቅሶ የሶማሊላንድ ዕውቅና መሻት በአፍሪካ ፖለቲካ ታሪክ የተለየ እንደሆነ ገልጾ ህብረቱ ጉዳዩን ለሌሎች ችግሮች በር ከፋች አድርጎ ከመመልከት ይልቅ ከተጨባጭ ታሪካዊ ሁኔታ፣ ሞራል እና የህዝቡ ፍላጎት አንጻር ተመልክቶ በተለየ ሁኔታ መፍትሔ ሊያገኝ የሚገባ የተለየ አይነት ሁኔታ እንደሆነ ገልጿል።

ከላይ የተጠቀሰው እንዳለ ሆኖ ምንም እንኳን ከዚህ በታች የተዘረዘሩት እውነቶች ህጋዊ ዕውቅናን ለሶማሊላንድ አጎናጽፈዋል ባይባልም ኢትዮጵያን ጨምሮ ሶስት (3) ሀገራት ቆንጽላ ጽ/ቤት ያላቸው ሲሆን ኬኒያ እና ግብጽን ጨምሮ ስድስት (6) ሀገራት የተወካይ ጽ/ቤቶች ከፍተው በዚህች እራሷን ሀገር ብላ ባወጀች ሀገር ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ አድርጌ መርጪያቸዋለሁ ካለቻቸው ፕሬዝደንት ጋር እየተነጋገሩ እና ውል እያሰሩ ግንኙነት ሲያደርጉ ከርመዋል፡፡ በእርግጥ የነዚህን ጽ/ቤቶች መከፈት ሱማሊያ ሉዓላዊነቴን የሚጥስ ነው ስትል በተደጋጋሚ አምርራ በዓለምአቀፍ ሚዲያዎች ስታወግዝም ይታያል።

More stories

አብን ዶ/ር በለጠ ሞላን የፓርቲው ሊቀመንበር አድርጎ ሰየመ

April 7, 2025

በትግራይ የሲቪል ጊዚያዊ አስተዳደር እንዲቋቋም አራት የትግራይ ተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲዎች ጠየቁ

September 17, 2024

የአፍሪካ ሕብረት – ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላላት ተሳትፎ እውቅና ሰጠ

October 15, 2024

የቡድን ሰባት አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ጉዳይ የይሁንታና የስጋት ቅልቅል መግለጫ ሰጡ

April 21, 2024

ከዚህ በተጨማሪ ሌላው አሻሚ ነገር በዓለምአቀፉ ማኅበረሰብ ሀገር ለመባል በተባበሩት መንግሥታት አባል ሀገራት እውቅና ማግኘት የማይቀር አስፈላጊ ቅድመሁኔታ ነው ወይስ አይደለም የሚለው ይህ ነው የሚባል ሥምምነት አለመኖር ነው።

ኢዜማ የፓርቲው ፕሮግራም ላይ << ኢዜማ ከጎረቤት ሀገሮች ጋር የሚኖረን ግንኙነት በጋራ ደኅንነትና ጥቅም ላይ በመመስረት በፍጹም መተባበር ላይ እንዲሆን፤ የኢኮኖሚ ትሥሥር በማጠናከር ከፍ ያለ የፖለቲካ ትበብር እንዲኖር የሚሰራ ይሆናል፡፡ መንግሥታት በሥምምነት ያጸደቋቸው ዓለምአቀፍ ህጎችና ሥምምነቶች በሁሉም ሀገራት እንዲፈጸሙ፣ የሀገራችን ሉዓላዊነት እንዳይገሰስ፣ ደካማው በጠንካራው እንዳይጠቃ፣ የተባበሩት መንግሥታት ፍትሃዊ የውሳኔ መስጫ አግባብ እንዲኖረውና እንዲጠናከር፣ የአፍሪካ ሕብረት ድርጅት በሁሉም መስኩ ጎልብቶ ዋንኛው የአፍሪካ ችግር ፈቺ ወሳኝ ኃይል ሆኖ እንዲወጣ የሚያደርግን እንቅስቃሴ በሙሉ የሚደግፍ ይሆናል፡፡>> ሲል ይጠቅሳል።

በፕሮግራሙ አንቀፅ 4.2.3 ላይ በግልፅ እንዳስቀመጠው ‹‹ ከዓለም አቀፍ ሕግጋትና ከታሪክ አንጻር አገራችን ራስዋ ባለቤት ሆና የምታስተዳድረው (sovereign ownership) የባህር በር እና መተላለፍያ (ኮሪዶር) የማግኘት መብት ሊኖረን እንደሚገባ ኢዜማ ያምናል፡፡ ከአካባብያችን እና ከሃገራችን ልዩ ሁኔታ አንጻር ሲታይ ደግሞ ይህን መብት የማስከበር ጉዳይ የኢኮኖሚ እድገት ብቻ ሳይሆን የሃገር ደህንነት እና የሃገር ህልውና ጉዳይ ነው ብሎ ያምናል፡፡ ይህን በሠላማዊ፣ ህጋዊና እና ዲፕሎማሲያዊ መስመር ብቻ ተግባራዊ ለማድረግ ይሰራል፡፡ ›› ይላል፡፡

በመሆኑም መንግሥት ይህንን መብት ለማረጋገጥ ሌሎች ጎርቤት ሀገራት ጋር በበቂ ሁኔታ እንዲያውቁ መደረጉን ቢገልጽም ጉዳዩ ከፍ ያለ የብሔራዊ ጥቅም በመሆኑ ዜጎች በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ማድረግ እና ሥምምነቱ ተፈጸመ ሲባል ከብሔራዊ ጥቅም ይልቅ የፖለቲካ አንድምታ ካላቸው እና ብዥታ ከሚፈጥሩ ዘገባዎች የመንግሥት ሚዲያዎች እንዲቆጠቡ እንጠይቃለን፡፡ በዓለም አቀፍ ቦታዎችም በበቂ ሁኔታ ዕውቀትን፣ ብቃትን እና ወጥነትን በተላበሰ መልኩ የዲፕሎማሲ ሥራ እንዲሰራ ጥሪ እናቀርባለን። በተጨማሪም መንግሥት ሌሎች አማራጭ የባህር በሮችን ለመጠቀም ከሌሎች ሃገራትም ጋር ውይይት ማድረጉን አጠናክሮ እንዲቀጥል እንጠይቃለን። ከዚህ ጋር በተያያዘ በተለይም ክልሎች ሕገመንግሥቱን በጣሰ መልኩ የፌደራል ሥልጣን የሆነውን የውጪ ግንኙነት ጉዳይን በቀጥታ ሲፈጽሙ የሚስተዋል ሲሆን ይህ የሃገሪቱ ሉዓላዊነት ላይ ይዞ የሚመጣው ችግር የከፋ ሊሆን ስለሚችል በቶሎ እርምት እንዲደረግ እንጠይቃለን።

ይህን መሰል ጉዳዮች ውጤታማ እንዲሆኑ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ሊሰራ የሚገባው ዋነኛው ጉዳይ የውስጥ ሰላማችን ጉዳይ ነው፡፡ ሀገራችን በታሪክ ሂደት ብሔራዊ ጥቅሞቿን ማስከበር የተሳናት በውስጣችን ባለ አለመረጋጋት መሆኑን በመረዳት የዜጎችን ሰላምና ደህንነት በማስከበር ሃገሪቱ ውስጥ ያሉ ችግሮችን በትኩረት ቅድሚያ ሰጥቶ በውይይት እና መሰል ሁነቶች ለመፍታት መንግሥት ከፍተኛውን ጥረት ሊያደርግ እንደሚገባ ልናሳስብ እንወዳለን።

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)

ጥር 09/ 2016 ዓ.ም.

POLITICS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
Ethiopia Makes a Bold Diplomatic Move to Have Access to Sea – by Aiming at Mutual Benefit with its Neighbor
የኤርትራ አምባሳደር ከአገሯ ለቀው እንዲወጡ ዩናይትድ ኪንግደም አዘዘች
Related posts
  • Related posts
  • More from author
POLITICS

ኢራን እኛ ላይ ምን ልታደርግ ትችላለች?

March 28, 2026
POLITICS

አስቸኳይ የአርበኛነት ጥሪ ለኢትዮጵያን

March 4, 2026
POLITICS

ትራምፕ ኢራንን እንደሚወጉ ፍንጭ ሰጡ

January 28, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2