Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  POLITICS  በሶማሌና በአፋር መካከል ተከስቶ የነበረው ግጭት ቆመ
POLITICS

በሶማሌና በአፋር መካከል ተከስቶ የነበረው ግጭት ቆመ

Ethioreview newsEthioreview news—September 13, 2024
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በሶማሌና በአፋር ክልሎች መካከል ተከስቶ የነበረው ግጭት እንዲቆም መደረጉን ችግሩን ለመፍታት የተቋቋመው ብሔራዊ ኮሚቴ አስታወቀ። 

ብሔራዊ ኮሚቴው ባደረገው ግምገማ የመጀመሪያው ምዕራፍ አፈጻፀም ውጤታማ ሆኖ በመገኘቱ ወደ ሁለተኛው የትግበራ ምዕራፍ ለመሸጋገር የሚያስችለውን ውሳኔ አሳልፏል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የሰላም ሚኒስትር አቶ ብናልፍ አንዱዓለም እና የሁለቱ ክልሎች ፕሬዚዳንቶች እንዲሁም የፌደራልና የክልል የፀጥታና ደኅንነት አካላት በተገኙበት የኮሚቴው የመጀምሪያ ምዕራፍ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

በድንበር ይገባኛል ጥያቄ ምክንያት በሶማሌና በአፋር ክልሎች መካከል ተከስቶ የነበረው አለመግባባት ወደ ግጭት አምርቶ ለብዙ ዜጎች የህይወት ህልፈትና ስደት እንዲሁም ለበርካታ ሀብትና ንብረት ውድመት ምክንያት መሆኑ የሚታወስ ነው።

ብሔራዊ ኮሚቴው ለኢፕድ በላከው መረጃ፣ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት እንዲቻል ከሁለቱ ክልሎችና ከፌደራል መንግሥት የፀጥታና ደኅንነት አካላት የተውጣጣ ብሔራዊ ኮሚቴ ተቋቁሞ ሲሰራ መቆየቱን በሪፖርት ጠቅሷል።

ብሔራዊ ኮሚቴው በመጀመሪያው ምዕራፍ የአፈፃፀም ሂደት ውስጥ በቀጣናው የነበረውን ግጭት የማስቆም፣ የሰዎችን ሞት የመከላከል፣ በግጭት አካባቢዎች ነፃ ቀጣና እንዲኖር የማስቻል እና ነፃ ቀጣናው በመከላከያና በፌደራል ፖሊስ ቁጥጥር ሥር ሆኖ እንዲቆይ የማድረግ ቁልፍ ዓላማዎችን ይዞ ተንቀሳቅሷል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጦፌ መሐመድ እንዳሉት፥ በብሔራዊ ኮሚቴው እና በሁለቱ የክልል መንግሥታት በኩል የተጀመረው የሰላም ጥረት በአካባቢው ተቀስቅሶ የነበረው ግጭት እንዲቆም አድርጓል።

ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ይቻል ዘንድ በሁለቱ ክልሎች አመራሮች መካከል በመተማመንና በወንድማማችነት ስሜት ችግሮችን ለመፍታት እየተደረገ ያለው ጥረት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባውም ጠቁመዋል።

የአፋር ብሔራዊ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ፥ ኮሚቴውን የሚመሩ የፌደራል ከፍተኛ አመራሮች፣ የዐቢይ እና የቴክኒክ ኮሚቴው አባላት እና በሁለቱ ክልሎች ውስጥ የሚገኙ አመራሮች እንዲሁም ሰላም ወዳዱ የአፋርና የሶማሌ ህዝብ በአካባቢው የነበረው ግጭት ወደ ሰላማዊ ሁኔታ እንዲመለስ ላበረከቱት የጎላ አስተዋፅኦ ያላቸውን አክብሮት ገልፀዋል።
 
በሁለቱም ክልሎች በኩል የሚስተዋሉ አፍራሽ አመለካከቶችን እየታገሉና እያረሙ መሄድ የየክልሎቹ ከፍተኛ አመራሮች ድርሻ መሆኑን ያወሱት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በመጀመሪያው ምዕራፍ የአፈፃፀም ሂደት ውስጥ የታየው ውጤት አበረታች ነው ብለዋል።

በሁለቱም ክልሎች በኩል የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በቅንነት እያረሙ መሄድና የተጀመረው በመተማመን ላይ የተመሰረተ የመፍትሔ አቅጣጫ ዳር እንዲደርስ መረባረብ እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል። 

የሰላም ሚንስትሩ ብናልፍ አንዱዓለም፥ ብሔራዊ ኮሚቴው ሲቋቋም ያነገባቸው ግጭትን የማስቆም፣ የሰዎችን ሞት የመከላከል፣ ነፃ ቀጣናን የመፍጠርና በነፃ አካባቢዎች የፌደራል የፀጥታ ኃይሎች እንዲሰፍሩ የማድረግ ቁልፍ ተልዕኮዎች ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል ደረጃ ተፈፃሚ ሆነዋል ብለዋል።

ይህም የአካባቢው ህዝብ የሰላም አየር እንዲተነፍስና እፎይታ እንዲያገኝ ያስቻለ መሆኑን ተናግረዋል።

በሁለቱ ክልሎች አመራሮችና የፀጥታ ኃይሎች በኩል የሚስተዋሉ ጥቃቅን ክፍተቶች እንዳሉ የጠቆሙት አቶ ብናልፍ፤ ነፃ ቀጣናውን ለቀው ያልወጡ ታጣቂ ኃይሎች በአስቸኳይ አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ማድረግና ችግሩ ዘላቂ መፍትሔ እስኪያገኝ ድረስ በአወዛጋቢ ቀጣናዎች ውስጥ ሰፈራዎችን ከማድረግ መቆጠብ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። 

የመጀመሪያው ምዕራፍ አፈፃጸም ስኬት ወደ ሁለተኛው ምዕራፍ ለመሸጋገር የሚያስችል ምቹ ሁኔታን የፈጠረ መሆኑንም አስረድተዋል።

የኢፌዲሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በበኩላቸው፥ በአካባቢው የተገኘው አንጻራዊ ሰላም በሁለቱ ክልሎች አመራሮች ጥረትና የሰላም ፍላጎት የተገኘ በመሆኑ ጅምሩ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና ችግሩ ዘላቂ መፍትሔ እንዲያገኝ ክፍተቶችን እየደፈኑ፣ ሥጋቶችን እያረሙና በህዝቦች መካከል ያለውን የወንድማማችነት ስሜት እያጠናከሩ መሄድ ያስፈልጋል ብለዋል።

ለዚህ ደግሞ በሁለቱም ክልሎች እጅ የሚገኙ ምርኮኞችን መለዋወጥ፣ ሂደቱን በሚያደናቅፉ አካላት ላይ እርምጃ መውሰድ፣ በውይይትና መግባባት ችግሮችን እየፈቱ መሄድ፣ የሰላም ስምምነቱን ሊያደናቅፉ ከሚችሉ አስተሳሰቦችና ድርጊቶች መቆጠብና ችግሮችን በፍጥነት እየፈቱ ለመሄድ መረባረብ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በመጨረሻም ዐቢይ ኮሚቴው በመጀመሪያው ምዕራፍ የተንጠባጠቡ ተግባራት በቶሎ እንዲፈፀሙ፤ የሁለተኛው ምዕራፍ ትግበራም እንዲጀመር በሙሉ ድምጽ ወስኗል።

ሰብዓዊ ድጋፎችን አጠናክሮ መቀጠል፤ ተፈናቃዮችን ወደ ቦታቸው መመለስ፣ የፖለቲካ ውይይቶችንና የህዝብ ለህዝብ መድረኮችን መፍጠር እንዲሁም በእርቅ ችግሩን እየቋጩ መሄድ ኮሚቴው በሁለተኛው ምዕራፍ ትኩረት ከሚሰጣቸው ቁልፍ ተግባራት መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውን ለኢፕድ የላከው መረጃው አመልክቷል።

መሰከረም 3 ቀን 2017 ዓም ENA

POLITICS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ፍር ድቤቱ “በቂ የሆነ ህጋዊ ምክንያት የለም” ሲል በኦሊምፒክ ኮሚቴ ላይ የተጣለው የዕግድ ውሳኔ በሙሉ ገለበጠ
የኢትዮጵያ አየር መንገድን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ተንቀሳቅሰዋል በተባሉ ግለሰቦች ላይ ክስ ተመሰረተ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
POLITICS

ኢራን እኛ ላይ ምን ልታደርግ ትችላለች?

March 28, 2026
POLITICS

አስቸኳይ የአርበኛነት ጥሪ ለኢትዮጵያን

March 4, 2026
POLITICS

ትራምፕ ኢራንን እንደሚወጉ ፍንጭ ሰጡ

January 28, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2