By Frew Getachew
“ሶማሊያ ፈርክሳለች” ይላሉ አቶ አብዱል መሐመድ። Failed state ናት ማለታቸው ነው። ሶማሊያ በ5 ፌዴራላዊ ግዛቶች ተከፋፍላ የየራሳቸው አለቆች የሆኑ ጎሳዎች የሚገዟት አገር ነች። የሚገርመው የፌዴራል ግዛቶቹ ድንበር ከአገሪቷ ድንበር በላይ የተጠበቀ ነው። አንዱ በአንዱ ላይ ድርሽ የለም። ሞቃዲሾ ያለውን ሐሰን ሼክ መሐመድንማ እርሱት።
ታዲያ እነዚህ የፌዴራል ግዛቶች በአገሪቱ “ፓርላማ” ውሳኔ ላይ የራሳቸው ድምጽ አላቸው። የእከሌ ከእከሌ ይበልጣል የሚባል የለም። ሁሉም ይናገራል። ሁሉም መሰማት አለበት። Everybody has a price እንዲሉ። ለዚህም ነው የሱማሊያ ፓርላማ “የእንትን ገበያ” ነው የሚባለው።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ነው እንግዲህ ትናንት እንደ ሰበር ዜና የወጣው ከ5ቱ የሦስቱ የኢትዮጵያን መውጣት መቃወም ለኢትዮጵያ ትልቅ “ብሥራት” የሆነው። ደቡብ ምዕራብ፣ ጁበላንድና ፑንትላንድ ናቸው ከኢትዮጰያ ጎን የቆሙት። እዚህ ላይ ደግሞ የሱማሌላንድን ጉዳይ እንጨምርበት።
ለማንኛው ወሬው እንዲህ ይላል
“Three out of Somalia’s five regional governments—Southwest, Jubbaland, and Puntland—have openly endorsed Ethiopia’s involvement in the new AUSSOM peacekeeping mission in Somalia. They have publicly opposed any attempt to expel Ethiopian forces without broad consensus. If this situation persists, it could ignite a chain of events that spirals into widespread unrest, engulfing Somalia and destabilizing the entire Horn of Africa.”
“ካላስ” ይላል ሱማሌ።
በሌላ በኩል ሐሩን ማሩፍ ሌላ “ሰበር ዜና” ይዞ ብቅ ብሏል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ለቢቢስ ከሰጡት ቃሀ መጠይቅ ላይ ነው የወሰደው። “ጠቡ የወደብ ከሆነ እኔ ለኢትዮጵያ የታጁራን ወደብ ለመስጠት ዝግጁ ነኝ። ይህንንም ለቻይና አፍሪቃ ጉባኤ ቤጂንግ ስንገናኝ ለሁለቱም እነግራቸዋለሁ” እያለች ነው ጅቡቲ
“Djibouti’s Foreign Minister Mahmoud Ali Youssouf says his country has a proposal which could solve the dispute between Somalia and Ethiopia.
He told the BBC his country is proposing giving Ethiopia access to the sea and, “a hundred percentage port management,” and a new corridor that is already built. He said it will the port of Tadjoura, a 100KM from the border with Ethiopia.
So the access to the sea for Ethiopia will not be a problem, he said.
Youssouf said President @IsmailOguelleh will have a chance to discuss the proposal with the leaders from the two countries during the Summit for China and African leaders next week.”
ኢትዮጵያ በሶማሌላንድ ያላትን የቆንስላ ቢሮ በአምባሳደር ደረጃ አሳድጋለች። ከሞቃዲሾ እኩል ማለት ነው። በአንድ አገር ሁለት አምባሳደር የመሾምን ፖለቲካዊ አቅጣጫ የፖለቲካ ሀሁ የሚያውቅ ሁሉ ይገነዘባል። ጨዋታው ከንግድ ወደብ ፍላጎት የዘዘለና ጂኦ ፖለቲካዊ አቅምን የማጎልበቻ መንገድ ነው። “ምስኪን” ሐሰን ሼክ መሐመድ አገሪቱን የproxy ጦርነት ሜዳ አድርጓት ሶማሊያ መቼም አገር የማትሆንበትን መንገድ እየጠረገ ነው።
ይመቸው!!
……..
በነገራችን ላይ :-
ሱማሌላንድ ከሶማሊያ የሚመጡ ሰዎች ያለ ቪዛ ወደ ሱማሌላንድ እንዳይገቡ እያሰበችበት ነው አሉ። ከሶማሊያ ወደ ሱማሌላንድ በቪዛ
….
This is interesting!!

