ቤላሩስ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላት የቤላሩሱ ፕሬዝዳንት አሌክሳንደር ሉካሼንኮ አስታወቁ። ፕሬዚዳንቱ ይህን ያሉት ከኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ጋር ተገናኝተው ምክክር ባደረጉበት ወቅት ነው። የትራክተርና የሌሎች ኢንጂነሪንግ ቁሳቁሶችን ለማምረት ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
የቤላሩስ ፕሬዝዳንት አሌክሳንድር ሉካሼንኮ ሀገራቸው ወሳኝ ቴክኖሎጂዎችን ለኢትዮጵያ ለማሸጋገር እና በእነዚሁ ቴክኖሎጂዎች ዜጎቿን ለማሠልጠን ዝግጁ መሆኗን ለኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ አረጋግጠዋላቸዋል።
ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ወደ ቤላሩስ ያቀኑት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተላከ መልዕክትም ለቤላሩስ ፕሬዚዳንት አድርሰዋል።
“ለኢትዮጵያ አስፈላጊ የሆኑ የኢንጂነሪንግ ምርቶችን በተሟላ መልኩ ለማቅረብ ፍላጎቱ አለን” ያሉት ፕሬዚዳንቱ የእርሻ ማሽነሪዎችን እና መሳሪያዎችን ለማምረትና። ተዛማጅ ቴክኖሎጂዎችን ለኢትዮጵያ ለማጋራት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። አክለውም ባለሙያዎችን ለማስለጠን ቃል ገብተዋል።
ለኢትዮጵያ መሪ ያላቸውን ከፈተኛ ክብርና ቤላሩስ በሁሉም መስክ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር ለማሳደግ እንደምሰራ ያመለከቱት ፕሬዚዳንቱ፣ “Mr Minister, let me reiterate: we are very eager to enhance our cooperation with your country,” “ክቡር ሚኒስትር ልድገመው፣ ከአገርዎ ጋር ያለንን ትብብር ለማሳደግ ከፍተኛ ጉጉት አለን” ሲሉ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለጌዲዮን ጢሞቲዎስ ማረጋገጫ መስጠታቸውን የቤልታ ዘገባ ያስረዳል።
ቤልታ ቀደም ሲል እንደዘገበው፣ በጥቅምት 2024 አሌክሳንደር ሉካሼንኮ በካዛን ከሚካሄደው BRICS የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አሊ ጋር ተገናኝተዋል። የቤላሩስ ርዕሰ መስተዳድር ስለ ትብብር ልማት ሲናገሩ “እኛ በደንብ በመተዋወቅ እንጀምር ። ሆኖም ፈጣን እርምጃ ለመውሰድ ደጋፊ ነኝ ። ዓለም በፍጥነት እየተቀየረ እና በፍጥነት እንድንንቀሳቀስ እየገፋፋን ነው ። ስለዚህ እኛ የምንስማማበትን ማንኛውንም እርምጃ ለመውሰድ በተዘጋጀህ ፍጥነት ለመንቀሳቀስ ዝግጁ ነን” ብለዋል ።
ፕሬዚዳንቱ ቤላሩስ የብሪክስ አባል እንድትሆን ኢትዮጵያ ላበረከተችው አስተዋጾ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። አክለውም ይህ ድጋፍ በቀጣይም እንደማይቋረጥ ተስፋቸውን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት ውል አስራ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ከጀመረች በሁዋላ የእርሻ መሳሪያዎችን ለማምረት የሚያስችላትን ስምምነት ከቤራሉስ ጋር ማድረጓ መንግስት እርሻ ላይ የጀመረውን ሰፊ ስራ አስፈቶ ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑን የሚያሳይ እንደሆነ አመላካች መሆኑ ተመልክቷል።
ፕሬዝዳንቱ “ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ለኛ በጣም አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል አንዷ ናት፡፡ ከሶቪዬት ዘመን ጀምሮ መልካም ትውስታዎች እና ለወደፊት ትብብር መልካም ተስፋዎች አሉን፡፡ ለእናንተም ጠቃሚ ሆነን እንገኝ ዘንድ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ለራሳችን የሚሆን ቦታ እናማትራለን” ብለዋል፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቴዎስ በበኩላቸው አሌክሳንደር ሉካሼንኮን የመገናኘት እድል ስላገኙ አመስግነዋል። በነበራቸው ቆይታም መደሰታቸውን ጠቅሰው ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድና እና ከኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት የተላከውን ምስጋናና መልዕክት አቅርበዋል።
በሁለቱ አገራት መካከል ጠንካራ፣ ባህላዊ እና ታሪካዊ ግንኙነት መንገንባቱ አውስተው፣ ቀደም ሲል በርካታ ኢትዮጵያዊያን ተማሪዎች በስኮላር ሶቪየት ሕዝብረት መማራቸው የዚሁ ታሪካዊ ግንኙነት አካል መሆኑ ጠኡመዋል። ይህ ግንኙነት አሁን ድረስ የቀጠለ መሆኑንም አክለዋል። ይህ ኝኙነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

