በጨራሽ ችግር ሑለት የውድድር ዓመታት ዋንጫ ማግኘት ያልቻለው የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የቪክቶር ዮኬሬሽን ዝውውር በሙሉ ስምምነት ማጠናቀቁን ዘ አትሌቲክ አረጋገጠ። ደጋፊዎች ጥያቄያቸው መልስ ያገኘ ይመስላል።
መድፈኞቹ ተጫዋቹን በ 63.5 ሚልዮን ዩሮ እና ተጨማሪ 10 ሚልዮን ዩሮ ክፍያ ለማስፈረም ተስማምተዋል። ስዊድናዊው አጥቂ ቪክቶር ዮኬሬሽ አሁን ላይ የጤና ምርመራውን እንዲያደርግ ከስፖርቲንግ ሊዝበን ፍቃድ ተሰጥቶታል።
ተጨዋቹ በነገው ዕለት ወደ አርሰናል የሚያደርገውን ዝውውር ለማጠናቀቅ የጤና ምርመራውን ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል። ቪክቶር ዮኬሬሽ በአርሰናል ቤቴ ታሪካዊውን የቴሪ ሄንሪ 14 ቁጥር ማልያ ለብሶ እንዲጫወት እንደተዘጋጀለት ተገልጿል።
ሌላው ፈራሚ ክርስቲያን ሞስኬራ ምን አይነት ተጨዋች ነው ?
መድፈኞቹን የተቀላቀለው ክርስቲያን ሙስኬራ እግርኳስ ከመጀመሩ በፊት ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ስፖርት የገባው በቅርጫት ኳስ ተጨዋችነት ነበር። 12ዓመቱ የቫሌንሺያን እግርኳስ አካዳሚ የተቀላቀለው ተጨዋቹ ከሶስት አመታት በፊት ለዋናው ቡድን መጫወት ችሏል።
መድፈኞቹ ጥሩ የመከላከል እውቀት ያለው እና ወደኋላ ተመልሶ ሽፋን መስጠት የሚችል ወጣት ተከላካይ አግኝተዋል። የ 21ዓመቱ ሞስኬራ የሚገጥሙትን ፈተናዎች በመገመት ጥሩ ምላሽ መስጠት የሚችል እና በአንድ ለአንድ ግንኙነቶች ጠንካራ መሆኑ ተገልጿል።
ተከላካዩ ኳሶችን በማሸነፍ የተወጣለት ቢሆንም ያገኘውን ኳሶ ይዞ ሲቆይ እና ኳስ ይዞ ሲጫወት የሚታይ ተከላካይ አይደለም። ተጨዋቹ የአርሰናልን የቀኝ መስመር ተከላካይ ቦታ በማጠናከር የዊሊያም ሳሊባ ተጠባባቂ ሆኖ ያገለግላል።
ተጨዋቹ ከዚህ በፊት በሶስት እና አራት ተከላካዮች አጨዋወት ተሰልፎ የተጫወተ ሲሆን ጥሩ የሚባል ጊዜም አሳልፏል። ክርስቲያን ሙስኬራ ያለው የእግርኳስ ችሎታ ሲገመገም ለአርሰናል እቅድ እና ታክቲክ የተስማማ መሆኑ ተገልጿል። ተጨዋቹ ባለፉት ሁለት የውድድር አመታት ከየትኛው ጉዳት ነፃ ሆኖ የቆየ ሲሆን 56 ተከታታይ የላሊጋ ጨዋታዎች ማድረግም ችሏል።



