በኦሮሚያ በተለይም ገለልተኛ የሆኑትን ልሂቃን ሲያነጋግር የቆየው የእነ ጃዋር ከትህነግ፣ ሻዕቢያና በጀነራል ምግበ ይመራል ከሚባለው ፋኖ ጋር ህብረት የፈጠሩበት ምክንያት ታወቀ። በኦሮሞ ድርጅቶች መካከል ይጀመራል የተባለው ድርድር እነ ጃዋርን አስቆጥቷል።
ኢትዮሪቪው ባገኘችው መረጃ መሰረት እነ ጃዋር በኦሮሚያ መንግስት ውስጥ ሰርገው በመግባት መንግስት ለማፍረስ ዕቅድ ነድፈው ነበር። ጃዋር ኦሮሚያ ካለው ሴሉ ጋር ሆኖ ከኬንያ ሲመራው ለነበረው ኦሮሚያን የማፍረስ ዕቅድ ውስጥ ታዬ ደንደአ እና እሱ የመለመላቸው ተባባሪዎች ነበሩ።
እንደ መረጃ ሰዎቹ ከሆነ በቅርቡ ከኦፌኮና ኢነግ ወደ ብልጽግና ከፈለሱት ውስጥ የዞንና ከዚያ በላይ አመራሮች ይገኙበታል። እነዚህን አካላት በበታች መዋቅር ውስጥ ማለትም በወረዳና ቀበሌ ማስረግ ነበር ዕቅዱ። በዚሁ መሰረት ሰፊ ቁጥር ያላቸው የኦፌኮና ኦነግ የመካከለኛ አመራሮችን ወደ ብልጽግና እንዲተሙ ሲደረግ የክልሉም ሆነ የፌደራሉ የመረጃ ክፍሎች ያውቁ ነበር።
ጃዋርና ባልደረቦቹ ባቀዱት መሰረት ከኦነግና ከኦፌኮ በርካታ አባላት አመራር ላይ ያሉት ሳይቀሩ ወደ ብልጽግና እንዲያመሩ ሲደረግ የዝውውሩን ወይም ፍlሰቱን ዓላማ የሚያውቁ ጥቂት ብቻ ቢሆኑም እነሱም ልባቸው ከእነ ጃዋር ጋር አልነበረም።
በዚሁ አግባብ ወደ ብልጽግና የኮበለሉት የኦነግ የዞን አመራር እንዳሉት ከሆነ ብልጽግናን የሚቀላቀለው የሁለቱ ድርጅቶች አባላት መበርከታቸው “ነገሩ ምንድን ነው” አሰኝቷቸው ነበር። ከኦፌኮም ሆነ ኦነግ አመራሮች በኩል ብስጭት እንደነበረም፣ ፍልሰቱ በተለይ ኦነግን ባዶ ስላደርገው በኃላፊዎች ደረጃ ሳይቀር አቤቱታ አስነቷል።
በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ “ጋላን እናጥፋ፣ የጋላን መንግስት እንንቀል፣ ቤተመንግስታችን ርስታችን ነውና እንረከበው” ወዘተ ማስፈራሪያዎችና ወለጋ የአማራ እንደሆነ የሚያስታውቁ አዋጆችና የትጥቅ እንቅስቃሴዎች በኦሮሞ ማህበረሰብ ዘንዳ የፈጠሩትን ስጋት ተከትሎ ሕብረት መፈጥር አግባብ እንደሆነ በአብዛኛው በሚባል ደረጃ አቋም የተያዘበት እንደሆነ ያነጋገርናቸው ቀደም ብለው አስታውቀውን መዘገባችን የሚታወስ ነው።
“ብልጽግና ውስጥ ሆነው ፓርቲውን ለመብላት፣ የበታቹን መዋቅር ለመሰርሰር ለተያዘው ዕቅድ በጀት ተመድቦለት ሲደረግ የነበረው ዝግጅት ሁሉ ኢሊሌ ሆቴል ስብሰባ ሲደረግ መክሸፉ የጃዋር ፕሮጀክት በኪሳራ መዘጋቱን አበሰረ” የሚሉት የጉዳዩን አካሄድ የሚያውቁ ወገኖች፣ “ለካስ ጃዋር የሚያጫውታቸው ምልምሎቹ በዋናነት የሚጫወቱት ሌላ ጨዋታ እንደነበር ይፋ ሆነ” ሲሉ የጃዋርን የጉዞ አቅጣጫ ያስለወጠውን ምክንያት ማስረዳት ይጀምራሉ።
በትግሉ ወቅት ለአሰራር እንዲያመች በተሰጠው ዕድል የኦህዴድን የበታች መዋቅር ተቆጣጥሮ የነበረው ጃዋር፣ ዕቅዱ በተመሳሳይ ባሰረጋቸው ሰዎች አማካይነት የበታች መዋቅሩን ሰብሮ በኦሮሚያ መንግስትን ለመበተን ነበር። መረጃ ያጋሩን እንደሚሉት የጃዋርና ታዬ ደንደአ ግንኙነት የጀመረው ከዚህ ጊዜ አንስቶ ነው።
በየካቲት ወር ኢሊሌ ሆቴል የተደርገው ስብሰባ ላይ የኦፌኮና ኦነግ አመራሮችና በአብዛኛው በኦነግ የተጠቆሙ ተሰብሳቢዎች ነበር የተገኙበት። በዚሁ ስብሰባ ላይ ኦነግ የጋበዛቸውና የእሱኑ ዓላማ ያራምዳሉ የተባሉ ቢሆንም መንግስትን ከተቃዋሚ ኃይሎች ጋር የማስታረቅ ሚና በመስራት የሚታወቁ እንደሆኑ ዝግጅት ክፍላችን በወቅቱ ማጣራት አድርጎ ነበር። በስብሰባው ወቅት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ሰራዊት ስብሰባውንና የስብሰባውን ውጤት መግለጫ ተቃውሞ ባሰራጨው ጽሁፍ የመከላከያና የጋር ውስጥ ደህንነት አመራሮች በንግግሩ ወቅት መገኘታቸውን በነቀፌታ ጠቁሟል። እንግዲህ ምንጮቹ እንደሚሉት እነ ጃዋር ያወጡት ዕቅድ ውስጥ ከነበሩት ምልምሎች መካከል ዋናዎቹ እንዚህ ስብሰባ ላይ ታይተዋል።
በዚህ ብስጭት፣ በዚህ ንዴት ጃዋር በቀጥታ አዲስ ከተጀመረው የሻዕቢያ፣ ትህነግና በሁለቱ አካላት በሚመራው ከፊል ፋኖ በፈጠሩት ሕብረት ውስጥ ራሱን፣ ቀደም ሲል የተጣላቸውን ባልደረቦቹን መስሎ የተቀላቀለው።
አሁን ላይ በቀን ውስጥ በተደጋጋሚ በተለይም በአማርኛ ቅስቀሳና አመጽ የሚያሰራጨው ጃዋር ” የእኔን ብሎኝ ነበር ንቅናቄ” ተቀላቅሎ በገሃድ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን ከሕዝብና ከፓርቲያቸው የመነጠል ዘመቻ ላይ ተዋናይ የሆነው በዚሁ አግባብና መነሻ እንደሆነ ጉዳዩን የሚያውቁ አመልክተዋል። የ”እኔንም ብሎኛል ንቅናቄ” አስቀድመው ሹመኛ የነበሩና የተባረሩ፣ ስልጣን የተከለከሉ፣ ቀደም ሲል ህዝብን በዘርና በስፍራ በመለየት ለጅምላ እልቂት ሲያመቻቹ የነበሩ፣ እወንጀል የሚፈለጉ፣ ሚዲያ ላይ በአክቲቪዝም የአንድን ሕዝብ ህልውና ለማጥፋት ሲረባረቡ የነበሩና ጠቅላይ ሚኒስትሩን ‘ኦሮሞን ካደ’ በሚል ሲከሱ የነበሩ እንደሆኑ የቅርብ ጊዜ አንደበታቸውና ተግባራቸው ምስክር ነው።
በተገለጸው አግባብ ያኮረፉ፣ የሻዕቢያንና የትህነግን ጥሪ የተቀበሉ በጋራ በጀመሩት እንቅስቃሴ ውስጥ የገባው ጃዋር ዋና ምክንያቱ የስሌት መዛባትና የዕቅድ መክሸፍ ባስከተለበት ብስጭት እንደሆነ እንቅስቃሴውን የሚያውቁ ገልጸዋል።
“የኦሮሞ ትግል አስኳል ነኝ፣ ከግራኝ መሀመድ ቀጥሎ ተጽዕኖ ፈጣሪ ነኝ ” ሲል የነበረው ጃዋር ” ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ብለውኛል” በሚለው ንቅናቄ ውስጥ ተሳታፊ ሆኖ በታየባቸው አግባቦች እያካሄደ ያለው ዘመቻ ” ትህነኝ የማጠብ፣ የማጽዳት፣ የማጠንና ዳግም የመሞሸር ነው” ሲል ሞገስ በተደጋጋሚ ጥያቄ ካደረገና ከተረዳ በሁዋላ በሰጠው አስተያየት የራሱን ግምገማ አስፍሯል። ሞገስ ጃዋርን በዚህ ጉዳይ ጠይቆት ” እኔንም ይህን ብሎኛል” በማለት ጠቅላይ ሚኒስትሩን ሲኮንን እንደነበር የሚታወስ ነው።
ትህነግ የሰሜን ዕዝን በክህደት አጥቅቶ / ራሱ የመስከረው፣ ዓለም የሚያውቀው፣ ሰለባዎቹ የመሰከሩት፣ ደጋፊዎቻቸው በጀግንነት ስሜት ደጋግመው ያነሱት እውነት ነው/ የመጀመሪያውን ጦርነት ሲከፍት የገመገመው “በተቋቋመው የዲጂታል ወያኔ የሳይበር ጦር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን ከሕዝብ ለይተናል። በግድያውና በሰላም እጦቱ ሕዝብ ተሰላችቶ ትህነግ ይምጣ የሚል ድምዳሜ ላይ ደርሷል” በሚል ከገመገሙ በኃላ መሆኑን ያስታወሱ፣ ዛሬ ጃዋር የገባበት ንቅናቄ በተመሳሳይ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ከሕዝብ በመነጠል የጋራ ኃይሉ የአገር መከላከያን ለማፍረስ የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት እንደሆነ የመረጃው ምንጭ አመልክተዋል።
ወደ ብልጽግና ካመሩት የኦፌኮ የመካከለኛ አመራሮች መካከል ለዝግጅት ክፍላችን መረጃ በመሰጠት የሚተባበሩ እንዳሉት የአቶ ታዬ ቃለ ምልልስ የዚህ ብስጭት ውጤት ስለመሆኑ በልበ ሙሉነት ያስረዳሉ። ሲያስረዱም አቶ ታዬ ከጃዋር ጋር ገጥመው በነበረበት ወቅት ከተያዙት ዕቅዶች መካከል አንዱ ይህ ሲሆን ቀጣዩ የኦሮሚያ ባለስልጣናትን ማቆሸሽ ሲሆን ለዚህም ተከፍሏቸው የተዘጋጁና ኬንያ ካሉ የፋኖ ሚዲያዎች ጋር ቃለ ምልልስ ለማድረግ ቀጠሮ የተያዘላቸው ይገኙበታል።
በተለይም አቶ ሽመልስ አብዲሳ መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ መስማማታቸውን፣ እሳቸውና ጠቅላይ ሚኒስትሩ መካከል ምንም ዓይነት መግባባት እንደሌለ በማሳየት የክልሉን የበታች ካድሬ ግራ የማጋባት ስራ ለመስራት ሰፊ ዕቅድ ተይዞ እንደነበር እነዚሁ ውገኖች አስረድተዋል።
የኢሊሌ ሆቴል ተሰብሳቢዎቹ ስብባውን ካከናወኑ በሁዋላ በጋራ ያወጡት መግለጫ በዋናነት የስልጣን ክፍፍልን፣ የክልሉን የፖለቲካ ስልታን መካፈል፣ አዲስ አበባን በኦፎሳል ኦሮሚያ ስር ማድረግ በዋናነት የሚጠቅሱ ሲሆኑ፣ ኦነግ በገዳ የአስተዳደር ዘዴ የተቀኘ አስተዳደር እንዲመሰረት ሲጠይቅ፣ ኦፌኮ ደግሞ አጠቃላይ የፖለቲካ ምክክር የሚል አሳብ አዋቷል።
የኢሊሌ ሆቴሉን ስብሰባ መግለጫ በተመለከተ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ባወጣው መግለጫ ሶስት ነጥቦችን ያስቀመጠ ሲሆን አንደኛው ነጥብ የሰላም ሂደቱ በአግባቡ አለመከናወኑን የሚገልፅ ነው፡፡ ድብቅ አጀንዳ ያለው ስብሰባ መሆኑንና መንግስት በክልሉ የሽግግር መንግስት አጀንዳን አምጥቶ የተበላሸ ገፅታውን ለመገንባት በሚል ስብሰባውን እንዳከናወነ የጠቀሰው መግለጫው በተጨማሪም የኦሮሞ ፓርቲዎች ጥምረት እንዳይፈጥሩ የማድረግ አላማ እንዳለውም አስረድቷል፡፡ በተጨማሪም የኦሮሞ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን የመከፋፈል ሀሳብ ያለው መሆኑን ገልፆ የአቋም መግለጫውን እንደማይቀበለው ማስታወቁ አይዘነጋም፡፡
ሰሞኑን በኦሮሚያ ፓርቲዎች የጋራ ውይይት በማድረግ ቀደም ሲል በኢሊሌ ሆቴል የጀመሩትን ስራ ለመቋጨት ማሰባቸው መሰማቱን ተከትሎ ጃዋር መሀመድ በማህበራዊ አውዶቹ ላይ “የችርቻሮ ድርድር ጊዜው ያለፈበት የከፋፍለህ ግዛ ስልት ነው። ከእንግዲህ የሚሰራው የድህረ አብይ ሁሉን አቀፍ ውይይትና ድርድር ነው” ሲል ይፋ አድርጓል።
ብልጽግና ሳይል “አብይ ከወረደ በሁዋላ” ድርድር እንደሚደረግ ያስታወቀው ጃዋር ርዕዮት ሚዲያ በሚያስተባብረው የትህነግን የማይረሱ ሃጢያቶች የማጠብና የማጻዳት ዘመቻን ተከትሎ የተጀመረው አብይ አሕመድን ነጥሎ የማጥቃት ስትራቴጂ ሳይታወቀው ይፋ ማድረጉን በልጥፉ ስር ያመላከቱ አሉ።
አማራ ላይ ሲዝትና፣ አማራን ከፋፎ ለማሳነስ አገው፣ ቅማንት፣ ራያ ወዘተ እያለ በሚቆጣጠራቸው ሚዲያዎች ሰፊ ሽፋን ይሰጥ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው።



