ራሳቸውን የትግራይ የሰላም ኃይሎች ወይም TPF በሚል ስያሜ የሚጠሩት ታጣቂዎች እነ ዶክተር ደብረጽዩን በሚመሩት ኃይል ወስጥ የነበሩ 689 ተዋጊዎች ከነ ሙሉ ትጥቃቸው እንደተቀላቀሏቸው አስታወቁ። የተከዱት ክፍሎች በቡድንም ሆነ በተናጠል ያወጡት ማስተባበያ የለም።
በምስል፣ በቁጥርና በተመደቡበት ምድብ ተለይተው በዝርዝር የቀረቡት 689 ታጣቂዎች የእነ ደብረጽዮንን ቡድን ተለይተው የወጡት ለሰላም ባላቸው ቁርጠኛ አቋም እንደሆነ ተመልክቷል።
“በነፃ መሬት” የሚገኙ የትግራይ የሰላም ሃይሎች ትህነግን ታግለው ከክልሉ እንደሚያስወግዱ አመራሮቹ ሰሞኑን ይፋ ባደረጉት ቃለ ምልልሳቸው ላይ ይፋ ማድረጋቸው አይዘነጋም።
” ቡድኑ ትግራይን ለማተራመስና ኢትዮጵያን ለመውጋት ከኤርትራ መንግስት ጋር እየሰራ ነው ” በሚል የሚከሱትና ጦርነት ለሰለቸው ለመላው ትግራይ ሕዝብ ዳግም ጦርነት እየደገሰ ያለውን ይህን ቡድን ማስወገድ አማራጭ የሌለው መሆኑን አመራሮቹ አስታውቀውዋል። ስምረት የተሰኘው አዲሱ ፓርቲም “ዱርዬ” ሲል የሚጠራውና ህጋዊ ሰውነት የሌለውን ስብስብ መንግስት እርምጃ እንዲወስድበት መጠየቁ አይዘነጋም።
ትናንት ይፋ በሆነ መረጃ ከሃምሌ 1/2017 ዓ.ም ጀምሮ ባለፉት 3 ቀናት ብቻ 689 በላይ የህገወጡ ቡድን ተዋጊዎች ካምፓቸውን ጥለው “የሰላም ኃይል” የሚባሉትንና በትግራይ ነጻ መሬት ከሚገኙት ወገኖቻቸው ጋር ተቀላቅለዋል። እነ ምግበ ከሻዕቢያ ጋር አብረው ካሰባሰቡት ተዋጊ መካከል ጥለው በመውጣት የትግራይ ሰላም ሰራዊት/TPF/ መቀላቀላቸውን ራሳቸው ሲመሰክሩ በማህበራዊ ሚዲያዎች ታይቷል።
በዚሁ መሰረት ከሻዕቢያ ጋር ሆኖ ኢትዮጵያን ለመውጋት ካበረው ህገወጥ ቡድን ሸሽተው የመጡት
- ከአርሚ 24: 65 ወታደሮች
- ከአርሚ 43: 57
- ከአርሚ 44: 205
- ከአርሚ 22: 34
- ከአርሚ 26: 12
- ከአርሚ 50: 31
- ከአርሚ 60: 9
- ከአርሚ 92: 86
- ከአርሚ 15: 27
- ከአርሚ 31: 22 ወታደሮች
- ከአርሚ 33: 36
- ከአርሚ 35: 19
- ከአርሚ 42: 15 ወታደሮች
- ከአርሚ 11: 26
- ከአርሚ 13:- 7
- ከአርሚ 17: 11
- ከአርሚ 70 (ከሱዳንን ሸረሪና): 5 ወታደሮች
- ከአርሚ 8: 13
- 9 ወታደራዊ ኮማንድ በድምሩ 689 ተዋጊዎች ህወሃትን ከድተው ህወሃትን ለመታገል የተመሰረተውን የትግራይ ሰላም ሰራዊትን መቀላቀላቸው ይፋ ሆኗል።
የሻዕቢያ መኮንኖች በሃራ መሬት የሚገኘውን የሰላም ኃይል እነ ምግበ እንዲደመስሱ መመሪያ ሰጥተው እንደነበር መረጃው ያላቸው በይፋ መናገራቸው የሚታወስ ነው። በዚሁ መሰረት ባለፈው ሳምንት የዲሽቃ ጥቃት ሙከራ ተደርጎ በሽማግሌዎች ብርታት ወደ ሙሉ ጦርነት ሳይገባ መቆሙ የጀርመን ድምጽ ምስክሮችን ጠቅሶ መዘገቡ አይዘነጋም። ይህንኑ ተከትሎ የሰላም ኃይሎ አመራሮች ” በውይይት የማይሰማ ከሆነ በሚገባው ቋንቋ እናናግረዋለን” ብለው ነበር።


