የኢትዮጵያ መንግስት ለድርድር ፋልጎት ካለ እጆ ረዝም እንደሚዘረጋ ማስታወቁን ተከትሎ ኤርትራ በአሰብ አካባቢ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የጋማ ከብቶችና የጦር ተሽከርካሪዎችን ማስፈሯ ተሰማ። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ኃይል በማደረጃቷ “ልትወረን እያኮበኮበች ነው” በርማለት የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር አስታውቀዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አራተኛውን የመድመር መጽሐፍ ሲያስመርቁ ” ኢትዮጵያ በጂኦግራፊ የተዘጋች አገር ሆና ለመጪው ትውልድ እንድተተላለፍ የሚፈቅድ ካለ እሱ የሞት ነው” በማለት ሲናገሩ ” ጦርነት አያስፈልግም” በሚል ማናቸውንም ዓይነት ድርድር ለማድረግፍ ዝግጁ መሆናቸውን፣ የሚመለክታቸው ወገኖች ሳይረፍድ ወደ ድርድር ካልመጡ የወደብ ጉዳይ አይቀሬ መሆኑንም በግልጽ አስቀምተው ነበር።
ኢትዮጵያ በግፍ የተወሰደባትን የአሰብ ወደብ ለማስመለስ የጀመረችውን ዘመቻና ዝግጅት “በተግባር ላይ የማይውል” ያሉት የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር “ኢትዮጵያ ልትወረን እያኮበኮበች ነው” ሲሉ ከሰዋል።
ከከሱ ጎን ለጎን የኤርትራ ጦር ራሱን እያዘጋጀና የጦር ተሽከርካሪዎችና ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን የጋማ ከብቶች አሰብ አቅራቢያ እያከማቸ እንደሆነ የመረጃ መንጮች ከአፋር ገልጸዋል።
ብዙ ቁጥር ያላቸው ግመሎችና አህዮችን በአሰብ በኩል ከኢትዮጵያ ድንበር በግምት 45 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ያከማቸው ሻዕቢያ ቀደም ሲል አሰብ ወደብ ዙሪያና አካባቢ የአየር መቃወሚያዎች መትከሉ አይዘነጋም። መቃወሚያዎቹ በኢትዮጵያ አየር ኃይል ሙሉ በሙሉ ተለይተው መታየታቸውም በተመሳሳይ መገለጹ አይዘነጋም። ኢትዮጵያ በበዛት አጥፍቶ ጠፊ ድሮኖች ለዚሁ ተግባር እያመረተች እንደሆነም አስተያየት ሲሰጥ ሰንብቷል።
ሻዕቢያ ከወራት በፊት በአስብ በኩል ጥቃት ይፈጸምብኛል በሚል አለኝ የሚለውን ኃይል ቢያሰልፍም፣ አላማው ከተሳካ ከትህነግ ጋር በመሆን የጅቡቲን መንገድ መቁረጥ በመሆኑ ኢትዮጵያ ዘመናዊና መካናይዝድ ኃይል በትይዩ ማስፈሯም ከአፋር እማኞች አስረድተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ” ዛሬ የኛ የሆነውን ቀይ ባህር መልሶ ለመጠየቅ የሚሰጋ ፣ የሚጠራጠር ትውልድ መፈጠሩ የስነልቦና ስብራት አካል ነው፤ አንችልም ብሎ ነው የሚያስበው፤ እኔ ላረጋግጥላችሁ እውዳለሁ ኢትዮጵያ ትችላለች “ ማለታቸውን “ዕንደራ” ወይም በትርጉሙ በስሜት የሚከወን፣ ውጤቱ የማያምር፣ ለከንቱ ልፋት የሚዳርግ ጉዞ በማለት ኤርትራ ብትቃወምም አለኝ የምትለውን የጦር ቁሳቁስ ወደ አሰብ ማጋጋዝ ከጀመረች፣ ጡረታ የወጡ ወታደሮች ሳይቀሩ ከተት እንዲጠሩ ማድረጓ በተደጋጋሚ መዘገቡ ይታወሳል።
በኢትዮጵያ በኩል አጠቃላይ ዝግጅት ስለመኖሩ እንጂ ዝርዝር መረጃ አይነገርም። በቅርቡ የአገሪቱ ጄነራሎች በየፊናቸው በሰጡት መግለጫ የዲፕሎማሲው ስራ ማለቁን፣ ኢትዮጵያ አሰብን ለመውሰድ የህግ፣ የታሪክ፣ የዓለም ዓቀፍ መርህና እንደሚደጋፋት አንስተው ጉዳዩ የማይቀር መሆኑን ማስታወሳቸው አይዘነጋም።
አሜሪካ የስቴት ዲፓርትመንት ከፍተኛ አማካሪ ማሳድ ቡሎስን፣ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ጋር ተገናኝተው በተለያዩ ጉዳዮች መምከራቸውን ተከትሎ ‟…ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ላደረጉልኝ መልካም አቀባበል ምስጋናዬ የላቀ ነው። የአፍሪካ ቀንድ ወሳኝ የሰላም ዘብ እና የአሜሪካ ወሳኝ አገር ከሆነችው ኢትዮጵያ ጋር በመቀናጀት የቀጠናውን ሰላም ለማስጠበቅ የጋራ መግባባት ላይ ደርሰናል…“ ሲሉ ተደምጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይም በተመሳሳይ በግል የማህበራዊ ገጻቸው ላይ ከማሳድ ቡሎስን ጋር መወያየታቸውን ጠቅሰዋል። ከዚህ ቀደም የአሜሪካ የመከላከያ ከፍተኛ ኃላፊዎችና ከተቅላይ ሚኒስትር አብይና ከኢትዮጵያ የመከላከያ አመራሮች ጋር ባደረጉት ውይይት ኢትዮጵያ ያቀረበችውን የቀይ ባህር ጥያቄ መቀበላቸ ተተቅሶ መዘገቡ አይዘነጋም። ከፍተኛ የጦር መኮንኖቹ ወደ ኢትዮጵያ ያቀኑት ሶማሊ ላንድ አሜሪካ ትሰፍርበታለች በተባለበት የበርበራ ወደብ ላይ ቦታ መረጣ ካካሄዱ በኋላ መሂኑ በከፍተኛ ደረጃ ጉዳዩን አጉልቶትም ነበር።
የኢትዮጵያና ኤርትራ ድንበር አሰብ ዙሪያ ውጥረቱ ባየለበት በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ መንግስት ለከፍተኛ የሰራዊቱ አመራሮች የጄነራልነት ማዕረግ መስጠቱ ታሰምቷል።
በተደጋጋሚ ሽሰፊ ቁጥር ያለው ሰራዊት በየዘርፉ በማስመረቅ የኢትዮጵያን መከላከያ በባህር፣ በአየር፣ በየብስና በዘመናዊ ትጥቅ እያዘመነ ያለው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ካሁን በሁዋላ ቀጥታ ውጊያ የሚገጥሙ አገራት ካሉ ሙሉ በሙሉ የቴክኖሎጂ ውጊያ እንደሚያደርግ በተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ መስጠቱ አይዘነጋም።

