Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  ዩኤስ አይዲ በመዘጋቱ በድብቅ እየከፈሉ መረጃ የሚያገኙ ሚዲያዎች ወሬ እያጡ ነው
News

ዩኤስ አይዲ በመዘጋቱ በድብቅ እየከፈሉ መረጃ የሚያገኙ ሚዲያዎች ወሬ እያጡ ነው

Ethioreview newsEthioreview news—September 22, 2025
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ነዋሪነቱ ከኢትዮጵያ ጎረቤት አገሮች በአንዱ ያደረገና ለጊዜው በስም ባልገለጸው አንድ ሚዲያ ይሰራ የነበረ ሪፖርተር ገቢው መንጠፉን ለባልደረቦቹ ሲያስረዳ ” ዩኤስ አይዲ መዘጋቱ እርዳታ ሲሰጣቸው የነበሩትን ሚዲያዎች ኪስ በማድረቁ ገቢዬ ቆሟል” ማለቱ ተሰምቷል። እሱ ብቻ ሳይሆን ሌሎችም በተመሳሳይ አገር ቤት ሆነው በእነዚሁ ተደጓሚ ሚዲያዎች ውስጥ በግልጽና በድብቅ ሲሰሩ የነበሩ ተቀንሰዋል። ላመጡት መረጃ ይከፈላቸው የነበሩ ግንኙነታቸው ተበጥሷል።

“አዲስ አበባ ካለው ቢሮ በእኔ ስር ሲሰሩ የነበሩ ሶስት ሪፖርተሮች በገንዘብ እጥረት ተባረዋል” የሚለው የዛሬው የጎረቤት አገር ነዋሪ ለዝግጅት ክፍላችን ተባባሪ እንዳለው መረጃ ያቀብሉ የነበሩም ግንኙነታቸው ተቋርጧል።

የመንግስት ሚዲያዎች ውስጥ ከሚሰሩ የሚዲይሳ ሰዎች በክፍያ በድብቅ ዜናና የውስጥ ደብዳቤዎች ያገኙ እንደነበር የሚናገረውና አሁን ላይ በሩዋንዳ የሚኖረው ሌላው “ጋዜጠኛ ” እንዳለው አሁን ላይ ሁሉም በሚባል ደረጃ መረጃ መሸጥ አቁመዋል። ምክንያቱ ደግሞ ከዩኤስ አይዲ መዘጋት ጋር ተያይዞ ሚዲያዎቹ ኪሳቸው በመራቆቱ ነው።

“በመንግስት ሚዲያ ውስጥ በክፍያ መረጃ ማግኘት የተለመደ ነው” የሚለው የሩዋንዳው ነዋሪ አሁን ላይ ጠብመንጃ ያነሱ የብሄር ድርጅቶችና እነሱን በሚያስተባብሩት በኩል በሚረዱት ሚዲያዎች በአንዱ ይሰራል።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

ለዝግጅት ክፋላችን ቅርብ የሆኑና ይህን መረጃ በስፍራው በማሰባሰብ የላኩልን እንዳሉት፣ መረጃ የሰጡዋቸው አካላት እንዳሉት በስፋት መረጃ በማግኘት ይታወቁ የነበሩት ሚዲያዎች አሁን ላይ እንደ ቀድሞው ጥሬ መረጃ አያገኑም። ምክንያቱም ከላይ የተገለጸው ነው።

“ዩኤስ አይዲ በመዘጋቱ በድብቅ እየከፈሉ መረጃ የሚያገኙ ሚዲያዎች ወሬ እያጡ ነው” በማለት ያስታወቀው ዩጋንዳ በስደት የሚኖረው ሪፖርተር አሁን ላይ ቡና በመሸጥ እንደሚተዳደር ይናገራል። ምን አልባትም ወደ አገሩ ሊመለስ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል።

በሩዋንዳ የሚገኙ የተለያዩ የዩቲዩብ ሰራተኞች፣ በኢትዮጵያ የብሄር ብጥብጥን ስፖንሰር በሚያደርጉ የሚታወቁ አገሮችና ተባባሪዎቻቸው እንደሚደጎሙ ያስታወቀው የሩዋንዳው ነዋሪ፣ ኬንያ ብዙ ምቾት ስለማይሰጥ ወደ ሩዋንዳ ማምራታቸውን መናገሩን መረጃውን ከላኩት ወገኖች ለመረዳት ተችሏል። ያም ሆኖ ኬንያ ውስጥም ሆነው የሚሰሩ እንዳሉም አክለው ገልጸዋል።

“ይናበባሉ” የሚሉት የሚዲያዎቹን አሰራር የሚከታተሉ ወገኖች፣ አዲስ አበባ ሆነው ለነዚሁ ሚዲያዎች መረጃ የሚሸጡት የመንግስት ሰራተኞች ስጋት እንዳለባቸው ገልጸዋል።

” እኔ የምሰራበት ሚዲያ / ስሙ ለጊዜው ያልተገለጸ/ ሶስት ሰራተኞቹን ካባረረ በሁዋላ ድጋፍ በማጣቱ አሁን ላይ መረጃ አልባ ሆኗል። በፊት ከሚታወቅበት አግባብ አንጻር አሁን ላይ ባዶ ነው ማለት ይቻላል” ያለው የጎረቤት አገር ነዋሪ፣ ኤሊያስ መሰረት በፋክት ቼክ ብቻ ዳጎስ ያለ ጥቅም ያገኝ እንደነበር አመልክቷል።

ይኸው ምስክር ድጎማው ሲቆም እንደ ሌሎቹ ስማቸው ያልተጠቀሰ ነገር ግን የሚታወቁ ሚዲያዎች፣ ኤሊያስ መሰረትም በተመሳሳይ ያሰራቸው የነበረውን ሰራተኞቹን ማሰናበቱን ያወሳው ምስክር፣ በገንዘብ ችግር ሳቢያ መስራት የማይችልበት ደረጃ ደርሶ እንደነበር በራሱ የፌስ ቡክ ገጹ ላይ በይፋ ማስታወቁን በዋቢነት ያስረዳል።

ከዚያም በሁዋላ በስበስክሪፕሺን የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም ለማንሰራራት ብዙ ጥረት ማድረጉን የሚገልጸው ምስክር፣ ብረት ካነሱት ዘንዳ ቀጥተኛ ድጋፍ የማያገኙት ሌሎቹ ምን አማራጭ ሊከተሉ እንደሚችሉ ለጊዜው መረጃ አልሰጠም።

በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ የሚዲያ ባለሙያዎችን ሰብሰበው ሲያነጋገሩ ” የቢራና የአልክሆል መጠጥ ማስታወቂያ ይፈቀድልን፣ ገቢ የለንም፣ ከገበያ ልንወጣ ነው ወዘተ” በማለት ጥያቄ ያቀረቡ እንደነበር አይዘነጋም።

በኢትዮጵያ “ተገደለ፣ ፈነዳ፣ ወደመ፣ ፈረሰ፣ አለቁ፣ …” የሚሉ የሚጮሁ መረጃዎች የሚመረጡት አንድም ከሙያ ስነምግባር በማፈንገጥ፣ በሌላም በኩል ተመልካችና አድማጭ ለመሳብ የሚመረጥ አግባብ በመሆኑ እንደሆነ የዘርፉ ባለሙያዎች በተደጋጋሚ መናገራቸው አይዘነጋም።

በሌላ በኩል ግን እንደ ትልቅ ድካም የሚጠቀሰው የመንግስት ኮሙኒኬሽን መረጃ ላይ ተኝቶ፣ መረጃ ለሚያፈተልኩ እድሉን በመስጠት ኢትዮጵያዊያን ከውጭ አገር ቀላሉን ጉዳይ “ሰበር ዜና” እየተባሉ እንዲሰሙ በመፈቀዱ ወይም በመመቻቸቱ እንደሆነ በተለያዩ ጊዜያት አስተያየት የሚሰጥበት ጉዳይ ነው።

በተመሳሳይ ዜና የአሜሪካ ሬዲዮ መቋረጡ ለኢትዮጵያ የበረከት ያህል መሆኑን የሚናገሩ፣ የአሜሪካ ሬዲዮ ቀደም ሲል የኢትዮጵያን መከላከያ ሰራዊት “የደርግ ሰራዊት” በማለት እንዲበተንና ሜዳ ላይ ወድቆ እንዲለምን ትልቁን ኃላፊነት ወስዶ መስራቱን በቁጭት እያስታወሱ ለፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ምስጋና አቅርበው ነበር።

በቅርቡ በተደረገው የህልውና ጦርነት ከትህነግ ጎን ቆማ የነበረችው አሜሪካ በዩኤስ አይዲ በኩል ቀለብ ትሰፍርለት የነበረው ቪኦኤ አማርኛ፣ ትግርኛ፣ ኦሮሚኛና ሶማሊኛ ክፍለጊዜ ላይ ይሰሩ የነበሩ “ኢትዮጵያዊያን” በአገራቸው ላይ የፈጸሙት የክህደት ወንጀል ሊጣራና በልዩ ሁኔታ ተመርመሮ ለትውልድ እንዲቀመጥ የሚጠይቁ እየተደመጡ ነው።

በዚሁ የህልውና ዘመቻ ወቅት አማራ ክልልና አፋር ሲወድም። በርካታ ግፍና የጦርነት ወንጀል ሲፈጸም፣ ሰላማዊ ዜጎች ሲረሸኑ ሚዛን የሳተ ዜና ከማቅርብ በዘለለ ሰላባዎች የሚወንጅሏቸውን ክፍሎች ኢንተርቪው በማድረግ ነጻ የማውጣት ስራ ሲሰሩ እንደነበር ስምና አጀንዳውን እያነሱ የሞገቱ ጥቂት አይደሉም።

“ለአሜሪካ ጥቅም እሰራለሁ” ብለው በመፈረም በቪኦኤ የተለያዩ ቋንቋዎች ከሙያው መርህ በማፈንገጥ የአሜሪካንን ጥቅምና ፍላጎት ለማስፈጸም ሲሰሩ የነበሩ አዲስ አበባ ሲገቡ ካባና ልዩ ምስጋና ሲያቀርቡላቸው የነበሩ አካላት ይህን ለማድረግ ያነሳሳቸው ምክንያት በመርጃና ማስረጃ ሊሞገት እንደሚገባ በቁጭት አስተየየት የሚሰጡ እየበርከቱ ነው። በቪኦኤ ብቻ ሳይሆን በሌሎችም አገራት ድጋፍ የሚሰሩ ጸረ ኢትዮጵያ ሚዲያዎች ላይ ተመሳሳይ አቋም ያላቸው ጥቂት አይደሉም።


NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
የድርድር ጥያቄውን ተከትሎ ኤርትራ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የጋማ ከብቶችና የጦር ተሽከርካሪዎች አከማቸች
ሻዕቢያ ለኢትዮጵያ አዲስ የጥምር ፓርቲ ቦርድ ሊያቋቁምላት ነው፤ “ ከጉባዔው በፊት የኦሮሞ ፖለቲከኞች ተለያዩ” 
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2