የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የመጀመሪያውን የጉበት ንቅለ ተከላ ማዕከል ለማቋቋም ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሱ ተገልጿል።
የኮሌጁ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ሙሉቀን ተስፋዬ ላለፉት ጥቂት ዓመታት በኢትዮጵያ የጉበት ንቅለ ተከላ ማዕከል ማቋቋም ፕሮግራምን ሲመሩ ከቆዩት እና ትውልደ ኢትዮጵያዊ የጉበት ንቅለ ተከላ ስፔሻሊስት ከሆኑት ዶ/ር ቅድስት ኪዳኔ ጋር ተገናኝተዋል። በውይይታቸው ማዕከሉን ለማቋቋም አፋጣኝ እንቅስቃሴ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
ከኢትዮጵያ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ጋር በመሆን የንቅለ ተከላ ማዕከሉን ለማቋቋም የሚያስችል የጋራ አስተባባሪ ኮሚቴ ፈጥረዋል።
ፕሮግራሙ በወደፊት የንቅለ ተከላ አገልግሎት በሀገር ውስጥ ባለሙያዎች ሙሉ በሙሉ እንዲመራ የኢትዮጵያውያን ዶክተሮች እና ነርሶች ክህሎት ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለበት ተስማምተዋል።

