የብሪክስ ሀገራት በኒውክሌር ኃይል ዙሪያ የመጀመሪያውን የጋራ ስትራቴጂያዊ ሰነድ አጸደቁ ሰነዱ የዓለም የኒውክሌር ሳምንት መድረክ አካል ሆኖ በተካሄደ ስብሰባ ወቅት መጽደቁን የሩሲያ የኒውክሌር ኮርፖሬሽን ሮሳቶም ገልጿል።
ከብራዚል፣ ቬትናም፣ ግብፅ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ኢራን፣ ቻይና፣ ደቡብ አፍሪካ፣ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች፣ ኢትዮጵያ፣ ቱርክ እና የደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት ኅብረት የኢነርጂ ማዕከል የተውጣጡ ተወካዮች በጉባኤው ላይ መገኘታቸውንም አስታውቋል።
⚛️ በጸደቀው ሰነድ የተገለጹት ዋና ዋና የሥራ ዘርፎች፦
- የሰው ኃይል ማጎልበት፣
- ለኒውክሌር ኃይል ፕሮጀክቶች ፋይናንስ ማሰባሰብ፣
- የአቅርቦት ሰንሰለቶችን ጥንካሬ ማረጋገጥ፣
- የሬአክተር ግንባታን እና የኒውክሌር ነዳጅ ዑደት ቴክኖሎጂዎችን ማስተዋወቅ፤
- የኒውክሌር ኃይል የማኅበረሰብ ተቀባይነትን ለማስገኘት መሥራት።
- የብሪክስ የኒውክሌር ኃይል የጋራ መድረክ ሰላማዊ የኒውክሌር ኃይልን ለአካባቢ ምቹ የኃይል ምንጭ አድርጎ የማስተዋወቅ ኃላፊነት ተጥሎበታል። ከብሪክስ አባልና አጋር ሀገራት የተውጣጡ ዘጠኝ ኩባንያዎችና ኤጀንሲዎች ለመድረኩ የድጋፍ መግለጫ ፈርመዋል።
“የጋራ መድረኩ በመጀመሪያው ዓመት በመንግሥትና በግል ኩባንያዎች መካከል ልምድ፣ እውቀትና ቴክኖሎጂን በቀጥታ ለመለዋወጥ የሚያስችል ቦታ ሆኗል። አዳዲስ አባላት ወደ መድረኩ መቀላቀላቸው ግቦቻችንና እሴቶቻችን ቁጥራቸው እየጨመረ በመጣ ሀገራት ዘንድ ተቀባይነት ማግኘቱን የሚያረጋግጥ፣ አስፈላጊና ተምሳሌታዊ እርምጃ ነው” ሲሉ የሮሳቶም ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሌክሲ ሊካቼቭ ተናግረዋል።
ስፑት ኒክ


