ኢትዮጵያ ኤርትራን በተመለከተ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ያስገባችው ደብዳቤ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። ከቀደመው ይልቅ ጠንካራ ይዘትና አቋም የተንጸባረቀበት ሁለተኛው ደብዳቤ ለተመድ የተላከው በቅርቡት በኤርትራ መሪነት፣ በትህነግና ፋኖ ጥምረት በወልደያ አቅጣጫ የተሞከረው የተቀናጀ ጥቃት ከከሸፈ በሁዋላ መሆኑ ኢትዮጵያ ምን አስባ ነው? የሚል ጥያቄ እያስነሳ ነው። መንግስት ግን ንግግር እንዲቀድም ተማጽኗል።
በወልደያ አቅጣጫ በተለያዩ በሮች በፋኖ ስም ተከፍቶ የነበረው ጦርነት ሻዕቢያና ትህነግ በግልጽ የተሳተፉበት እንደነበርና አሁንም ድረስ ይኸው እንቅስቃሴ ቦታ እየለያየ የሚካሄድ መሆኑን የድርጅቶቹ ሚዲያዎችና ተባባሪዎች በይፋ እያስታወቁ ይገኛሉ። በተለይም የትህነግና የሻዕቢያ ሚዲያዎች እንደሆኑ የሚታወቁ በወቅቱ ጥቃቱን በሰበር ድል ሲቀባበሉት መሰነበታቸው አይዘነጋም።
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ኤርትራን በተመለከተ ለሁለተኛ ጊዜ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሳፉት ደብዳቤ ይህንኑ እውነታ ሉዓላዊነትን የመጋፋት ድርጊት እንደሆነ አመልክቷል። ከጀርባ የዕቅዱ ባለቤት ኤርትራ እንደሆነች አስታውቋል።
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ ለአንቶኒዮ ጉቴሬዝ የላከው ደብዳቤ ለሁለት አስርት ዓመታት “No war – No peace ሰላም አልባ፣ ጦርነት አልባ” ሆኖ የኖረውን የኢትዮጵያና የኤርትራ ግንኙነት በማስወገድ ረገድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የወሰዱትና ዓለም ያደነቀው እርምጃ አደጋ ላይ መውደቁን ያወሳል።
ኢትዮጵያ በለውጡ ማግስት የወሰደችው እርምጃ ተዘግቶባቸው ለነበሩ፣ ተለያይተው ለቆዩ ቤተሰቦች መልካም አጋጣሚ ሆኖ የትንግርት ያህል ዓለም ሲያወደሰው እንደነበር አይዘነጋም። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይም ይህንኑ ታላቅ ተጋባር በመፈጸማቸው የኖቤል ተሸላሚ መሆናቸው አይዘነጋም።
አሁን ላይ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳመለከተው የሃገራቱን ግንኙነት መርህ ተኮር በሆነ ዘላቂ ግንኙነትና ጥቅም ላይ ለመመስረት የተደረገው ጥረት ሁሉ በኤርትራ መንግስት የግትርነት እና የተለላኪነት ባህሪ ችግር እንደገጠመው አስታውቋል።
ደብዳቤ አክሎም “የኤርትራ መንግስት ፅንፈኛ የትህነግ አመራሮችን ጨምሮ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የተለያዩ ታጣቂዎችን በጦር መሳሪያ በመደገፍ ኢትዮጵያን ለማያባራ ቀውስና ትርምስ ለመዳረግ እየሰራ መሆኑን በመጥቀስ ኢትዮጵያ ኅልውናዋን በማረጋገጥ ሉዓላዊነቷን ለማስከበር አስፈላጊውን ሕጋዊ እርምጃ ለመውሰድ እንደምትገደድ አበክሮ ያስተነቅቃል።
በመጨረሻም ኢትዮጵያ ከቀይ ባህር የተገለለችበት መንገድ ቅቡልነት የሌለው በመሆኑ ኢትዮጵያ በሕጋዊ መንገድ የወደብ ባለቤት ለመሆን የያዘችው ጥረት አጠናክራ እንደምትቀጥል በደብዳቤው ያለማመንታት ግልጽ አድርጓል።
በኤርትራ መንግስት እና በትግራይ ህዝብ ነፃነት አውጪ ግንባር (ትህነግ) መካከል የተፈጠውን ጥምረት ወይም ጥምዶ በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ የተቀናጀ ጥቃት ለመፈፀም የተደረገ መሆኑ ያወሳው ደብዳቤው፣ ሁለቱ አካላት ኢትዮጵያ ላይ ጥቃት ለመፈጸም በዝግጅት ላይ መሆናቸውን “ደርሼበታለሁ” ብሏል። አክሎም ሁለቱ ቡድኖች እያደረጉ ያሉትን በመረጃ የተደገፈ ዝግጅት መታገስ የማይችልበት ደረጃ መድረሱን በመግለጽ “ሃይ በሉልኝ” ሲል ተማጽኗል።
ሰሞኑን በወልድያ ከተማ መውጫና መግብያ በሮችን ጨምሮ በተለያዩ የከተማዋ ቀበሌዎችና አከባቢዎች እነዚሁ ቡድኖች በቅንጅት ባቀነባበሩት የወረራ ሙከራ ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ መደረጉን ደብዳቤው ጠቁሟል። ውጥኑንም በግልጽ ቋንቋ በትህነግ እና በኤርትራ መንግስት ድጋፍ ነውጥ ለማካሄድ የተያዘ ውጥን እንደነበር አመልክቷል።
በተጠቅሱት አካባቢዎች ከታየው በከባድ መሳርያ የታገዘ ጦርነት መካሄዱን ተከትሎ የውጭ ጉዳይ ሚኒሰቴር ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞትዮስ የላኩት ጠንካራ ደብዳቤ ይህ እስከተጻፈ ድረስ በገሃድ ምላሽ አልቀረበበትም።
ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶንዮ ጉቴሬዝ ማክሰኞ፣ መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም የተላከው ደብዳቤ በትህነግ እና በተባባሪው የኤርትራ መንግስት መካከል በተፈጠረው ጥምረት ሳቢያ በአገር ሉአላዊነት ላይ አደጋ የሚጥል እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን በጥልቅ የሚያስረዳ ነው።
ጌድዮን ጢሞትዮስ በፃፉት ደብዳቤ፣ ቀደም ሲል በሁለቱም አካላት መካከል የተፈጠረውን ቅንጅት መንግስት መረጃ እንደነበረውና ይህንን መረጃ ለሰፊው ህዝብ ሰላም እንዲሁም የፌደራሉ መንግስት በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ተቀስቅሶ የነበረውን ግጭት ዳግም እንዳይቀሰቀስ በሚል ሲሆን፣ምንም እንኳን አካሄዳቸው ጸረ ሰላም ቢሆንም መንግስት በያዘው በዚሁ የሆደ ሰፊነት አቋሙ ሳቢያ በታጋሽነት ለማለፍ መገደዱን አስረድተዋል።
ጌድዮን አክለውም፣ በኤርትራ መንግስት ዋና ጠንሳሽነት እንዲሁም በትህነግ አስተባባሪነት በፋኖ ታጣቂ ሀይሎች ተዋናይነት በወልድያ ከተማ የተሞከረውን የአመፃ እንቅስቃሴ፣ እየተጠነሰሰ ያለውን ሴራ የተባበሩት መንግስት ድርጅት የተላዩ ኃላፊዎችና በይተለይም ለዋና ፀሐፊው አንቶንዮ ጉቴሬዝ “እወቁልን” ብለዋል።
በወልድያ እና አከባቢ ተቀስቅሶ በነበረው ግጭት አድማሱን እንዲሰፋ በማድረግና በተለይም በአንዳንድ የሕገመንግስት እና የይገባኛል ጥያቄ የሚነሳባቸው አከባቢዎች ግጭት ለመቀስቀስ ያለመ ተልእኮ እንደነበረው በመዘርዘር ሚኒስትሩ ለአንቶኒ ጉቴሬዝ በደብዳቤው ገልውላቸዋል።
ይሁንና፣ የከተማዋ ነዋሪዎች ባሳዩት ሆደ ሰፊነት የግጭቱን አድማስ በታቀደው ልክ ሳይስፋፋ እና በኤርትራ መንግስት እንዲሁም በትህነግ አንጃ ቡድን መካከል የተጠነሰሰው ሴራ ሳይሳካ መቅረቱን የገለፁት ሚኒሰትሩ፣ ይህም ኢትዮጵያ ወደ ቀይባህር ለመመለስ እያደረገችው ያለችውን ጥረት ለማደናቀፍ የተሸረበ ሴራ እንደነበር አመልክተዋል።
ለዚህ ተግባር የኢትዮጵያ የሉዓላዊነት የሚጥስና የማያከብር አለፍ ሲልም የትብብር መንፈስን የሚጥስ ተግባር በመሆኑ የዓለምዓቀፉ ማሕበረሰብ ጉዳዮን በአንክሮ እንዲከታተለው፣ እንዲሁም በዚሁ ስርዓት የጣሰ ተግባር ላይ እየተሳተፉ ያሉ አካላትን እንዲገስፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞትዮስ በደብዳቤያቸው ጠይቀዋል።
በተለያዩ ጊዜያቶች በኤርትራ መንግስት እና በትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪ ግንባር (ትህነግ) መካከል ሲፈጸሙ የቆዩትን የሽብር እንቅስቃሴዎች ምንም እንዃን የፌደራሉ መንግስት በቂ መረጃ ቢኖረውም ፣ በጋራ ለመስራት ካለው ጥልቅ ፍላጎት አንፃር ጉዳዮን በዝምታ ለማለፍ እንደመረጠ በደብዳቤው ላይ ተመላክቷል።
ይሁን እንጂ፣ በወልድያ ከተማ መግብያና መውጫ በር አከባቢዎች በተጠቀሱት ኃይሎችና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በፀጥታ ኃየሰሎች ላይ የተከፈውን ጥቃት የፌደራሉ መንግስት በአገር ሉአላዊነት ላይ የተቃጣ ጥቃት አድርጎ እንደሚመለከተው፣ መንግስትም በአጻፋው ለሚወስደው እርምጃ ውርድ ከራሴ ብሏል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞትዮስ ኢትዮጵያ እንደ አገር የቀይባህር ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እያደረገች ያለው ጥረት የሌሎችን አገራት ጥቅም ባከበረ፣ በውይይት እንዲሁም በመቀራረብ የሚከናወን መሆኑ በደብዳቢያቸው አምልክተዋል።
የአገሪቱ ርእሰ ብሔር ታዮ አፅቀ ስላሴ በበኩላቸው መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም የሕዝብ እንደራሴዎች የጋራ ምክርቤት ላይ የአዲሱ በጀት ዓመት መክፈቻ አስመልክተው ባደረጉት ንግግር የባሕር በር ጉዳይ አስመልክተው ኢትዮጵያ የማያወላዳ አቋም እንዳላት መግለፃቸውን አይዘነጋም። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይም ጉዳዩ ያለቀ መሆኑን ማስታወቃቸው የሚታወስ ነው።
ወደ ቀይ ባህር ለመመለስ ኢትዮጵያ ያቀረበቻቸው አመክንዮዎች በዓለማቀፉ ማሕበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት ማግኘቱ በተገለጸበት ቅጽበት፣ ራሳቸውን “በኢትዮጵያዊነት” የሚጠሩ ሚዲያዎችና በ”ጋዜጠናነት” ስም የሚታወቁ የኢትዮጵያን የባህር በር ባለቤትነት በመቃወም ሌርትራ በመወገን በግልጽ የውግዘት ዘመቻ ላይ እንዳሉ የሚታወቅ ነው።

