Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  POLITICS  በአማራ ክልል ዝርፊያ መፈጸሙና ንብረት መውደሙ ከመረጋጋት በሁዋላ የሕዝብ አጀንዳ ሆነ
POLITICS

በአማራ ክልል ዝርፊያ መፈጸሙና ንብረት መውደሙ ከመረጋጋት በሁዋላ የሕዝብ አጀንዳ ሆነ

Ethioreview newsEthioreview news—August 14, 2023
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የአማራ ክልል ተፈትሮ የነበረውን ቀውስ ተከትሎ ከፍተኛ አግባብነት የሌላቸው ድርጊቶች እንድተፈጸሙ እየተገለጸ ነው። በሰው ላይ የደረሰው ጉዳት በይፋ በገለልተኛ ወገን ባይጣራም ጉዳቱ ቀላል እንዳልሆነ እየተገለጸ ነው። ዝርፊያ ተፈጽሟል። ንብረት እንዲወድም ተደርጓል። አሁን ላይ ክልሉ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ በመግባቱ ህዝብ በሆነውና ባየው ጉዳይ በስፋት እየተነጋገረ እንደሆነ ተሰምቷል።

በድንገት በተባራሪ ጥይት ህይወታቸው ያለፈ በርካታ ንጽሃን፣ “ለምን ትግሉን አልተቀላቀላችሁም በሚልና የመንግስት አጋዥ ነህ” በሚል እርምጃ የተወሰደባቸውና በርካታ ዜጎች መኖራቸውን የሚጠቁሙ አሁንም መፍትሄው ጠብመንጃ በማንሳት በሰላም መወያየት እንደሆነ ይመክራሉ።

የአማራ ክልል ሚዲያ ኮርፖሬሽን ያነጋገራቸው ሲናገሩ እንደተሰማው ንብረት ማውደም የክሉን ህዝብ ስራ አጥነት የሚያባብስ፣ አንዳችም ፋይዳ የሌለውና ዓላማ ቢስ ተግባር ነው። ቤታቸው ራሳቸውን ሸሽገው የነበሩና አሁን ሰላም መውረዱን ተከትሎ የወድመውን ንብረት ለመመልከት እድል ያገኙ እጅግ ማዘናቸውን አስታውቀዋል። ንብረት የማውደም ፖለቲካ ጥቅሙና ግቡ ሊገባቸው እንደማይችል አመልክተዋል። ለአብነት በፍሎራ ጣና እና በደቡብ ወሎ የተፈጸመውን ሚዲያው እንደሚከተለው ዘግቧል።

ጣና ፍሎራ አበባ ልማት ከፍተኛ ውድመት የደረሰበት መኾኑን አስታወቀ

More stories

ደቡብ ሱዳን ስድስተኛ ሀገር ሆና የናይል ስምምነት ማዕቀፍን አጸደቀች

July 12, 2024

“ትህነግ ጦሩን እስጠግቷል፤ የጦርነት ስጋት አለብን” የጠለምት ወሰንና ማንነት አስመላሽ

June 7, 2025

“የኢትዮጵያን ህልውና የሚበይኑት የተፈጥሮ ሀብቶች…”

September 2, 2024

“ዘመን ትውልድን ይገነባል ፤ ትውልድም ዘመንን ይገነባል”

September 10, 2023

ባሕር ዳር: ነሃሴ 07/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ከሰሞኑ በአማራ ክልል በነበረው አለመረጋጋት ጣና ፍሎራን ጨምሮ በአካባቢው የሚገኙ ሌሎች አራት የኢንቨስትመንት ተቋማት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡

በአማራ ክልል በተፈጠረው አለመረጋጋት የሰው ሕይወት ጠፍቷል፣ አካል ጎድሏል፣ በንብረት ላይም ጉዳት ደርሷል፡፡ ከሰሞኑ በባሕርዳርና አካባቢው በነበረው አለመረጋጋት የአበባ ምርት አምራቹ ጣና ፍሎራ እና ሌሎች አራት ተቋማት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡

ጉዳት የደረሰባቸው ተቋማት ለበርካታ ሠራተኞች የሥራ እድል የፈጠሩ፣ ለሀገር የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኙ ተቋማት ናቸው፡፡

የጣና ፍሎራ የኢርጌሽን ሱፐርቫይዘር መኳንንት ወርቁ በጣና ፍሎራ ከአሥር ዓመታት በላይ እንደሠራ ነግሮናል፡፡ ጣና ፍሎራ ለበርካታ ዜጎች የሕይወት መሠረት የሆነ ነውም ብሏል፡፡ በጣና ፍሎራ ውስጥ ተቀጥረው የሚሠሩ በርካታ ሠራተኞች ሕይወት መስርተውበታል፣ ቤተሰብ ደግፈውበታል፡፡ ብዙዎችን አቅፎ የያዘው ተቋም ወድሞብናልም ነው ያለው፡፡

ጦርነት ለማንም እንደማይጠቅምና አውዳሚ መሆኑን የተናገረው መኳንንት በጦርነት ምክንያት ለሀገር ትልቅ አስተዋጽዖ የሚያደርገው ድርጅት ከፍተኛ ውድመት ደርሶበታል ነው ያለው፡፡ ጣና ፍሎራ ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ ለሀገር የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኝ እንደነበረም ተናግሯል፡፡ ችግሮችን በሰላም መፍታት እየተቻለ በተፈጠረው አለመረጋጋት መውደም የሌለበት ድርጅት መውደሙን ነው የገለጸው፡፡

ካለፈው ውድቀትና ውድመት በመማር ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ መፍታት ይገባል፣ ጦርነት ውድመት ከማምጣት ያለፈ ጠቃሚ አይደለምም ብሏል፡፡ ማንኛውም ሰው የጦርነትን አስከፊነት በመረዳት ሰላምን መስበክ እንደሚገባውም ተናግሯል፡፡ የአማራ ክልል ከጦርነት ሳያገግም፣ በጦርነቱ ምክንያት የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀያቸው ሳይመለሱ ያለ ክልል ነው ያለው መኳንንት አሁን ላይ ተጨማሪ ጉዳት እንዲደርስ ማድረግ ክልሉን የበለጠ ይጎደዋል ነው ያለው፡፡ የእርስ በእርስ ችግሮችን በውይይት መፍታት ግድ እንደሚልም ተናግሯል፡፡ ከንግግር ያለፉ አካሄዶች ማኅበረሰብን ይጎዳል ብሏል፡፡ ግጭት የሚያወድመው የራስን ሀብት እንደሆነም ገልጿል፡፡

ጣና ፍሎራ ከፍተኛ ውድመት ስለደረሰበት ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ እንዳደረጋት የተናገረው መኳንንት መልሶ ለማቋቋም ከፍተኛ ወጪ እንሚጠይቅም ተናግሯል፡፡ ችግሮች ቢፈጠሩ እንኳን ተቋማትን እንደ ግል ሃብት መጠበቅ እንደሚገባም ገልጿል፡፡ ለልጆች ሰላምን ማስተማር ይገባልም ብሏል፡፡

የጣና ፍሎራ ፕሮፓጌሽን ሱፐርቫይዘር ዓለም ፈጠነ በጣና ፍሎራ አሥርት ዓመታትን መሠራቷን ተናግራለች፡፡ ከጣና ፍሎራ በማገኘው ገቢ ደካማ ቤተሰቦቼን አስተዳደርላሁ ነው ያለችው፡፡ አሁን ላይ ግን እንደ ቤተሰብ የምናየው ጣና ፍሎራ ወድሞብናል ብላለች፡፡ ከለበስነው ልብስ ውጭ ምንም ሳንይዝ ሁሉም ጉዳት ደርሶብናል ነው ያለችው፡፡ ድርጅቱም ዘረፋና ወድመት እንደደረሰበት ነው የተናገረችው፡፡

እንደ ሠራተኛም እንደ ድርጅትም ከፍተኛ ጉዳት ነው የደረሰው ብላለች፡፡ ሰላም ካለ ሁሉም አለ፣ ሰለም ከሌለ ሁሉም የለም፣ ሁሉንም እንዳናጣ ሰላምን መጠበቅ ይገባል ነው ያለች፡፡ ከጦርነት የሚገኘው ውድመት ብቻ ነውም ብላለች፡፡

የጣና ፍሎራ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ጌታቸው ጨርቆስ ጣና ፍሎራ ከ13 ዓመታት በፊት 300 ሚሊዮን ብር ኢንቨስት ተደርጎበት የጀመረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ጣና ፍሎራ በየአመቱ ከ8 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ለሀገር የሚያስገኝ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ ጣና ፍሎራ አንድ ሺህ ቋሚ ሠራተኞችን ቀጥሮ ሲያሠራ እንደነበርም አስታውሰዋል፡፡

የደረሰው ጉዳት በባለሙያ የሚገመት ቢሆንም ጣና ፍሎራ እስካሁን ባለው ግምት ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት ደርሶበታል ነው ያሉት፡፡ የሌሎች ተቋማት ሲጨመር ጉዳቱ ከፍተኛ እንደሆነም ገልጸዋል፡፡ ጣና ፍሎራን በፍጥነት ወደ ሥራ ለመመለስ አስቸጋሪ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡ ጣና ፍሎራ የማኅበሰረብ አገልግሎት የሚሰጥ ተቋም መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ሰላምን በውይይት ማምጣት እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ ውይይት የማይፈታው ነገር እንደሌለም ገልጸዋል፡፡

በደቡብ ወሎ ዞን በተፈጠረ አለመረጋጋት በአንዳንድ አካባቢዎች ዘረፋና ውድመት መድረሱን የምሥራቅ አማራ ኮማንድ ፖስት አባልና የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አሥተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን አስታውቀዋል፡፡

የደቡብ ወሎ ዞን ሕዝብ እንደማንኛውም አካባቢ ማኅበረሰብ የልማት፣ የመልካም አሥተዳደር፣ የሥራ አጥነትና የኑሮ ውድነት ችግሮች ቢኖሩበትም ከመንግሥት ጋር በመተባበር እንደሚፈታለት ያምናል ሲሉ ዋና አሥተዳዳሪው በመግለጫቸው አስረድተዋል፡፡

እንደ አማራ ሕዝብም የማንነትና የወሰን እንዲሁም የህገ-መንግሥት መሻሻልና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ጥያቄዎች ስለመኖራቸውም አንስተዋል፡፡ እነዚህንም በታቀደ፣ ህጋዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እንዲፈታለት የሚሻ ታላቅ ሕዝብ ነው ብለዋል፡፡

በሰሜኑ ጦርነት ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበትን ሕዝብ መልሶ ለማቋቋም መንግሥት ሰፊ ሥራ እየሠራ ባለበት ሂደት ከጦርነት ማግስት ከሰላም አማራጭ ውጭ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን ህግና ስርዓት እንዲከበርለት ሕዝቡ በሠላማዊ ሰልፍ መጠየቁንም ዋና አስተዳዳሪው አውስተዋል፡፡

በመከላከያ ሠራዊቱ ላይ የተደረገውን የስም ማጥፋት ዘመቻም ሕዝቡ ማውገዙን ገልጸዋል፡፡ መከላከያ የሀገር አለኝታና የሉዓላዊነት መገለጫ ስለመሆኑም ሕዝቡ ከአሁን በፊት አካሂዶት በነበረው ሠላማዊ ሰልፍ ማረጋገጡንም ጠቅሰዋል፡፡

በማዳበሪያና ምርጥ ዘር ስርጭትና የእርሻ ሥራ ወሳኝ የልማት ወቅት ላይ አርሶ አደሩ በተረጋጋ መንገድ ሥራውን እንዳያከናውን በቅርቡ የተፈጠሩ አለመረጋጋቶች የልማት ሥራውን ከማስተጓጎላቸው በተጨማሪ የማኅበረሰቡን በሠላም ወጥቶ የመግባት እንቅስቃሴ መገደባቸውን ጠቁመዋል፡፡

በደቡብ ወሎ ዞንም በምዕራብ አካባቢ ባሉ አንዳንድ ወረዳዎች በተፈጠረው አለመረጋጋት ችግር የንብረት ዘረፋና ውድመት ደርሷል ብለዋል፡፡ በመካነ ሠላም ማረሚያ ቤት ዘረፋና ውድመት ደርሷል፡፡ ኅብረተሰቡንም የማጎሳቆል ሥራ ተሠርቷል፡፡ በአቀስታ ከተማ የመንግሥት ቢሮዎች ኮምፒውተርና ሌሎች የቢሮ ቁሳቁሶች ተዘርፈዋል ነው ያሉት ዋና አሥተዳዳሪው፡፡ ጃማ ደጎሎ ከተማም ተመሳሳይ ድርጊት መፈጸሙን ገልጸዋል።

በሌላ በኩል በአማራ ሳይንት ወረዳ ንብረት እንዳይዘረፍና የሰው ሕይወት እንዳይጠፋ ማኅበረሰቡ ተደራጅቶ የመከላከል ሥራ ሠርቷል፡፡ መሃል ሳይንትም ተመሳሳይ እንቅስቃሴ መኖሩን ጠቁመዋል ዋና አሥተዳዳሪው፡፡ በወግዲ ወረዳ ጥሩ እንቅስቃሴ መኖሩን ገልጸዋል። አልብኮ ወረዳም ከሌላ አካባቢ ለመዝረፍ የመጣ ቡድን ላይ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል፡፡

የዞኑ ሕዝብ ያልተገባ እንቅስቃሴን ባለመቀበል መከላከያ ሠራዊት ሕግ እንዲያስከብርለት እየጠየቀ ስለመሆኑ አስረድተዋል። ማዳበሪያም እንዲቀርብለት አርሶ አደሩ እየጠየቀ ይገኛል ብለዋል፡፡

የአካባቢው የፀጥታ ኃይልና አሥተዳደር ከመከላከያ ሠራዊቱ ጋር በመቀናጀት አለመረጋጋት የገጠማቸውን አካባቢዎች ወደቀደመ ሰላማቸው በመመለስ መደበኛና የልማት እና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች በተለመደው መንገድ እንዲከናወኑ ይደረጋል ብለዋል። መረጃው የደቡብ ወሎ ዞን መንግሥት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ነው።


  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ…
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት!
POLITICS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
የደም ማነስ ምልክቶች
የላሊበላ ሰላም የነዋሪዎቿ የልብ ትርታ – ከንቲባ ዲያቆን ተፋራ ሰይፉ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
POLITICS

ኢራን እኛ ላይ ምን ልታደርግ ትችላለች?

March 28, 2026
POLITICS

አስቸኳይ የአርበኛነት ጥሪ ለኢትዮጵያን

March 4, 2026
POLITICS

ትራምፕ ኢራንን እንደሚወጉ ፍንጭ ሰጡ

January 28, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2