Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  SOCIETY  ነጩ ወርቅ በወቅቱ እንዲሠበሠብ ሁሉም ርብርብ እንዲያደርግ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጠየቀ
SOCIETY

ነጩ ወርቅ በወቅቱ እንዲሠበሠብ ሁሉም ርብርብ እንዲያደርግ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጠየቀ

Ethioreview newsEthioreview news—October 15, 2024
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ለሰሊጥ አዝመራ የተመቸ አካባቢ ነው፡፡ በቀጣናው ነጩ ወርቅ እየተባለ የሚጠራው የሰሊጥ ምርት ለቀየው አርሶ አደሮች አንደኛ ደረጃ የሚባል የገቢ ምንጭ ነው፡፡ ምርቱ በተለይም ለውጭ ገበያም የሚቀርብ በመኾኑ የሚመለከታቸው አካላት በቅንጅት እስከ አዝመራ መሠብሠብ ድረስ የሚሠሩት ሥራ ነው፡፡

ነጭ ወርቅ እየተባለ የሚጠራውን ሰሊጥ ከሚያመርቱ ወረዳዎች መካከል ታች አርማጭሆ፣ ማዕከላዊ አርማጭሆ፣ ጠገዴ፣ አለፋ፣ ጣቁሳ፣ ጭልጋ፣ ነባሩ ጭልጋ፣ ምሥራቅ በለሳ፣ ምዕራብ በለሳ እና ኪንፋዝ በገላ ወረዳዎች ተጠቃሾች ናቸው፡፡

አርሶ አደር ይበልጣል አስተራይ በታች አርማጭሆ የሚኖሩ አርሶ አደር ናቸው፡፡ አርሶ አደሩ ዘንድሮ ለነጩ ወርቅ ትኩረት ሰጥተው ማሳቸውን መሸፈናቸውን ነግረውናል፡፡

አርሶ አደሩ እንደሚሉት በዚህ ዓመት ወደ አምስት ሄክታር የሚጠጋ የሰሊጥ አዝመራ እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡

በዚህ ዓመት በተቻለ መጠን ከግብርና ባለሙያዎች ጋር በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች ተጠቅመው በምክረ ሃሳብ ማሳቸውን በሰሊጥ መሸፈናቸውን ገልጸዋል፡፡

አሁን ላይ አዝመራው ሲታይ የተሻለ ምርት እንደሚያገኙ ሰብሉ ካለበት ቁመና ተነስተው ያላቸውን ተስፋ ነው የተናገሩት፡፡

አርሶ አደሩ ሰሊጥ እንደደረሰ ጊዜ የማይሰጥ እና በቶሎ መሠብሠብ ያለበት አዝመራ በመኾኑ አጋዥ ሰው ያስፈልገዋል ነው ያሉት፡፡

አሁን ላይ ሰብሉ ሳይበላሽ በፍጥነት ለመሠብሠብ ጥረት እያደረጉ ቢኾንም አጋዥ ኀይል የሚያስፈልገው በመኾኑ የጉልበት ሠራተኛ ቢፈልጉም የሰው ኀይል ማግኘት እንዳልቻሉ ነው የተናገሩት፡፡ በማዕከላዊ ጎንደር ዞን  አሁን ላይ የደረሰውን የሰሊጥ ሰብል ለመሠብሠብ የጉልበት ሠራተኛ እጥረት እንዳለም ነው የተገለጸው።

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሰብል ልማት ቡድን መሪ ዮሃንስ ተስፋየ አሁን ላይ የሚሠበሠበው የሰሊጥ ሰብል በመኽር ከተዘራው 75 ሺህ 277 ሄክታር መሬት ላይ የተዘራ መኾኑን ተናግረዋል።

በዞኑ ነጩን ወርቅ ለመሠብሠብ ችግሮች ማጋጠማቸውን ነው የነገሩን፡፡ አንደኛው አሁን ላይ ዝናብ የመዝነብ ሁኔታ ስላለ እና ይህም የደረሰውን የሰሊጥ ምርት ስለሚያረግፈው በፍጥነት መሠብሠብ እንዳለበት ነው ያስረዱት፡፡ አቶ ዮሃንስ የጉልበት ሠራተኛ ከቦታ ቦታ አለመንቀሳቀስ ሰሊጡን በጊዜው ለመሠብሠብ እንቅፋት መኾኑን አስገንዝበዋል፡፡

የሰብል ቁመናው በጥሩ ደረጃ ላይ የሚገኝ በመኾኑ እና ያለምንም ብክነት ሰብሉን ለመሠብሠብ እስከ 30 ሺህ የጉልበት ሠራተኛ ለዞኑ ብቻ እንደሚያስፈልግ ነው የተናገሩት፡፡ ምርቱን በሚገባ ሠብሥቦ ለሀገር ጥቅም ለማዋል ሁሉም የጉልበት ሠራተኞች እንዲንቀሳቀሱ ትብብር እንዲያደርግ አሳስበዋል፡፡ በዚህ ሥራ ላይ የጉልበት ሠራተኞች እንዲሳተፉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የሰሊጥ ልማቱ ላይ 24 ሺህ 526 በላይ አርሶአደሮች እየተሳተፉ እንደሚገኙ የገለጹት የሰብል ልማት ቡድን መሪው  ከዚህ ውስጥ 1 ሺህ 453 የሚኾኑት ሴቶች መኾናቸውን ተናግረዋል፡፡

ምርቱ በዓለም ገበያ አዋጭ በመኾኑ የምርት ብክነት እንዳያጋጥምም ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ ነውም ብለዋል።

በዞኑ ለምቶ ከሚሠበሠበው የሰሊጥ ሰብልም 602 ሺህ 216 ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ከዞኑ ግብርና መምሪያ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። (አሚኮ)

SOCIETY
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
“ሻማን ማን አቃጠለሽ ቢሏት… አቅፌ የያዝኳት ክር ናት” በደቡብ ጎንደር
በኮበለሉት ዶ.ር ፍስሐ እሸቱና ባልደረቦቻቸው ላይ የተመሰረተው ተደራራቢ ክስ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
SOCIETY

አስጨናቂዋን ሰዓት ወደ ደስታ የቀየረው የኢትዮጵያዊያን የሕክምና ባለሙያዎች ስኬት

August 23, 2025
News

በ2018 ጓደኞቼ ዩኒቨርስቲ ይገባሉ፤ በድህነት ከተማ ሄዶ መማር ይልቻለው ታዳጊ ለቅሶ!

August 22, 2025
SOCIETY

“በጠለምት ወረዳ በዝናብ እጥረት ሳቢያ እንስሳት እየሞቱ ነው፤ ሕዝብ እየተሰደደ ነው”

August 18, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • INTERVIEW
    • law
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • ያበደው
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2