ከሀዋሳ፣ ከወላይታ ሶዶ እና ከአካባቢው የመጡ በርካታ ደጋፊዎች መካከል አለመግባባት በመፈጠሩ የተነሳ ሊፈጠር የሚችልን አደጋ ለመከላከል ሲባል ጨዋታው በዝግ ስታዲየም እንዲካሄድ መወሰኑን ፖሊስ አስታወቀ። ፖሊስ መግለጫ ወይም መረጃ በወቅቱ ለመስጠት አለመቻሉ የሃሰት ወሬ እንዲሰራጭ በር መክፈቱን ጠቅሰው ይህ አገራዊ ድክመት በፍጥነት ሊታረም እንደሚገባው ሲገለትስ ነበር። ጃዋር የሃሰት ስም ሰጥቶት የገደለው ወጠት እናቱ ልጅሽ ሞቷል ተብለው ለቅሶ ላይ እንደነበሩ አስታወቀ።
ፖሊስ ግጭቱን ለማባባስ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ውስን ግለሰቦችን በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያጣራ ሲሆን ውጤቱንም በየጊዜው ለሕዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል። ፖሊስ በመግለጫው እንዳለው “በአንድም ሆነ በሌላው መልኩ የእርስ በርስ ግጭት የሚፈልጉ አካላት ሰው ሞቷል እያሉ የሚያሰራጩት ወሬ ሀሰተኛ መሆኑን እና በአንድም ሰው ላይ የሞትም ይሁን የአካል መጉደል ጉዳት ያልደረሰ መሆኑን አረጋግጧል” ብሏል።
ፖሊስም ሆነ የአገሪቱ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች መረጃ ለመስጠት አንዳቸውም አለመፍጠናቸው በርካቶችን አናዷል። በራሳቸው ተነሳሽነት የሃሰት መረጃውን ለመመከት ከሞከሩት በቀር በይፋ የሚታወቅ የመንግስት አካል ያልሞተ ሰው ሞተ እስኪባል ድረስ ዳተኛ መሆናቸው ካልታረመ አንድ ቀን አደጋ ሊያስከትል እንደሚችል እነዚሁ የተቆጡ ወገኖች ገልጸዋል።
ጃዋር “ሞተ” በማለት ስሙን ቀይሮ ሲቀሰቅስበት የነበረው ወጣት አብዮት ጩሎ ” ሞቷል እየተባለ ፎቶዬ በተሰራጨበት ማግስት የ2ኛ ዲግሪ መመረቂያ ፅሑፌን አቅርቤ መመረቄን አረጋግጫለሁ ! ” ሲል ሌላ ዓለም ውስጥ እንደሚገኝ አመልክቷል። እናቱና ራሱን አብቅቶ ወደ ሌላ ምዕራፍ ይሸጋገራል ያሉት ልጃቸው ሞት ስሙ ተይሮ በጃዋር አማካይነት መርዶ ደርሷቸው በምን ዓይነት ሃዘን ላይ እንደነበሩ አብዮት ዘርዝሯል። ፖሊስ ይህ ወንጀል ነው ዘግይቶም ቢሆን ቅጥፈት ሲል ያስታወቅው። ከፖሊስ መግለጫው ስር የአብዪት ምስክርነት ሰፍሯል።
ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የተሰጠ ወቅታዊ መረጃ

በትላንትናው ዕለት በአዲስ አበባ ስታዲየም በሲዳማ ቡናና ወላይታ ዲቻ መካከል የኢትዮጵያ ዋንጫ ፍጻሜ የእግር ኳስ ውድድር መካሄዱ ይታወሳል፡፡
ሁለቱን ክለቦች ለመደገፍ ከሀዋሳ፣ ከወላይታ ሶዶ እና ከአካባቢው የመጡ በርካታ ደጋፊዎች መካከል አለመግባባት በመፈጠሩ ጨዋታው በዝግ ስታዲየም እንዲካሄድ ተደርጎ ፖሊስ በደጋፊዎች መካከል ይፈጠር የነበረውን ግጭት በማስቀረት አስፈላጊውን ወቅታዊና ሕጋዊ ተግባር በመፈፀም ሕግና ሥርዓት አስከብሯል፡፡
ነገር ግን የሀገራችን ሰላምና መረጋጋት የሚመራቸው በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ያሉ አካላት ተናበው የሰዎች ሕይወት እንዳለፈ አስመስለው በመዘገብ ግጭት ለማባባስ እየሞከሩ እንደሆነ ታዝበናል፡፡
ፖሊስ ግጭቱን ለማባባስ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ውስን ግለሰቦችን በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያጣራ ሲሆን ውጤቱንም በየጊዜው ለሕዝብ ይፋ ያደርጋል። ከዚህ ውጭ በአንድም ሆነ በሌላው መልኩ የእርስ በርስ ግጭት የሚፈልጉ አካላት ሰው ሞቷል እያሉ የሚያሰራጩት ወሬ ሀሰተኛ መሆኑን እና በአንድም ሰው ላይ የሞትም ይሁን የአካል መጉደል ጉዳት ያልደረሰ መሆኑን አረጋግጧል፡፡
ስፖርት በባህሪው የተጣላን የሚያቀራርብ ሆኖ ሳለ በሁለቱ ደጋፊዎች መካከል የተፈጠረው አለመግባባት ወደ ሌላ እንዳይሰፋ ፖሊስ በወሰደው ህጋዊ እርምጃ ግጭቱን ተቆጣጥሯል፡፡
ይሁን እንጂ በሀሰተኛ ወሬ ሕብረተሰቡን ወደ ግጭት እንዲያመራ እና የሕዝብ አለኝታና ጠባቂ የሆነውን ፖሊስ ስም ለማጉደፍ በሚንቀሳቀሱት ላይ ፖሊስ ጥብቅ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድና በቀጣይም ስፖርቱ ለእንዲህ ዓይነት ሥርዓት አልበኝነት ተገዢ እንዳይሆን ፖሊስ ከሚመለከታቸው አጋር አካላት ጋር ተቀራርቦ እንደሚሰራ ያስታውቃል፡፡
” እናቴ ‘ ልጅሽ ሞቷል ‘ ተብላ እያለቀሰች ነበር ፤ ነገር ግን ቤተ ዘመድ ለቅሶ ከመቀመጡ በፊት እናቴንና ቤተሰቦቼን አረጋግቻለሁ ” – አብዮት ጩሎ
አብዮት ጩሎ ” ሞቷል እየተባለ ፎቶዬ በተሰራጨበት ማግስት የ2ኛ ዲግሪ መመረቂያ ፅሑፌን አቅርቤ መመረቄን አረጋግጫለሁ ! “
ትላንት የወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ቡድን ከሲዳማ ቡና አቻው ጋር የነበረው የኢትዮጵያ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ያለ ደጋፊ በዝግ ስታዲየም እንዲደረግ ከመወሰኑ ጋር በተያያዘ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ” በፀጥታ ሃይሎች ደጋፊዎች (የወላይታ ዲቻ) ተገደሉ ” እየተባለ መረጃዎች ሲሰራጩ ነበር።
ነገር ግን ክለቡ መረጃዎቹ ውሸት መሆናቸውንና ” አንድም ደጋፊ አለመሞቱን ” ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዛሬው ዕለት ባደረገዉ ተጨማሪ ማጣራት በርካቶች በማህበራዊ ትስስር ገፆች የተቀባበሉትና ” ሞተ/ተገደለ ” የተባለው ወጣት ጉዳይ ሀሰተኛ መረጃ መሆኑንና ወጣቱ በሕይወት መኖሩን ከራሱ አንደበት አረጋግጧል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከላይ በፎቶው የሚታየውንና ” ተገደለ / ሞተ ” ተብሎ በስፋት በማህበራዊ ሚዲያ የተወራበትን ወጣት አብዮት ጩሎ አገኝቶ አነጋግሯል።
” የወላይታ ዲቻ ቀንደኛ ደጋፊ ብሆንም በጨዋታው ዕለት ማግስት የ2ኛ ዲግሪ መመረቂያ ፅሑፌን የማቀርበብት ዕለት ስለነበር ወደ አዲስ አበባ አልሄድኩም ” ያለው አብዮት ” ነገር ግን ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ በበርካታ የማህበራዊ ሚዲያዎች ፎቶዬ እየተሰራጨ ‘በፀጥታ ሃይሎች ተገድሏል’ የሚል መረጃ ደጋግሜ ስመለከት በጣም ነበር የደነገጥኩት ” ብሏል።
በወላይታ ዲቻ የስፖርት ክለብ ማለያ የተነሳውና ብዙ የማህበራዊ ሚዲያዎች ያሰራጩት ፎቶ የራሱ ቢሆንም ፎቶውን ግን የተነሳው ትላንት እንዳልነበር አረጋግጧል።
” አሁን ላይ እኔም ተረጋግቻለሁ ” የሚለዉ ወጣት አብዮት ” በወቅቱ ወደ እናቴ ስደውል ‘ ሞቷል ‘ ተብላ እያለቀሰች ነበር ፤ ነገር ግን ቤተ ዘመድ ለቅሶ ከመቀመጡ በፊት እናቴንና ቤተሰቦቼን አረጋግቻለሁ ” ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።
” እኔ ‘ ሞቷል ‘ እየተባለ ፎቶዬ በተሰራጨበት ማግስት የ2ኛ ዲግሪ መመረቂያ ፅሑፌን ያቀረብኩበትና መመረቄን ያረጋገጥኩበት ነበር ፤ ፈታኞቼና አማካሪዎቼ በተረጋጋ መንፈስ ጥናታዊ ፅሑፌን እንዳቀርብ አግዘዉኛል ” ሲል አክሏል። ቲክቫኽ አብዮትን አነጋገሮ መረጃውን ስላካፈለን እናመሰግናለን።


