አቶ ታዬ ደንደአ ሰሞኑን በቅብብሎሽ እየተዘዋወረ በነበረው ቃላቸው መንግስት በተለይም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ የሰሜኑን ጦርነት እንዳስጀመሩ አስታወቅው ነበር። አቶ ታዬ በፖለቲካ ታሪካቸው የሚያውቋቸው በከፍተኛ ደረጃ ሲወቅሷቸው፣ በክህደት የሰሜን ዕዝን እንደመቱ መረጃ ሲቀርብባቸው የነበሩ የትህነግና የወቅቱ የሻዕቢያ መልዕክተኞች አሞካሽተዋቸዋል።
በተለይም የትህነግ ደጋፊዎች፣ አክቲቪስቶቻቸውና ሚዲያዎቻቸው፣ ሻዕቢያ የቀጠራቸው የሚታወቁ “ኢትዮጵያዊ ነን የሚሉ” በሚመሯቸው ሚዲያዎችና እነዚህኑ ተከትለው መረጃ የሚያሰራጩ የማህበራዊ ሚዲያ ተወዛዋዦች አቶ ታዬ የጀግና ስም እየሰጡ ሲያሞግሱ፣ በሰሜን ጦር ደምና አጥንት ሲዛበቱ፣ በኢትዮጵያ አለኝታዎች ደም ሲቆምሩ የትግራይ ክልል የፍትህ ቢሮ ሀላፊ የነበረውን አበራ ንጉሥን ምስክርነታቸውን ዳግም ሰጥተዋል።
ነብሳቸውን ይማርና አቶ ሴኮ ቱሬ፣ በሕይወት ያሉት ሊነናል ጀነራል ጻድቃን ገብረተንሳይ፣ የትግህነግ ሚዲያዎችና ደጋፊዎቻቸው፣ እንዲሁም የክህደቱ ሰለባዎች እንዴት እንደተጨፈጨፉ፣ እንዳምለጡና እንደተካዱ የተናገሩት ሁሉ ተረስቶ አቶ ታዬ ደንደአ አዲስ ትርክት ይዘው ሲመጡ አቶ አበራ ንጉሱ “ልክ አይደለም” ሲሉ መስክረዋል።
አቶ ታዬ ቀደም ሲል ኦፌኮ ነበሩ፡፡ ከኦፌኮ “አትረቡም” ብለው ወደ ወጣቶች ይዘው ወደ ጫካ ገቡ፡፡ ተያዘው ታሰሩ። ከዛም ኦህዴድን ተቀላቀሉ። ከዚያም ብልጽግና ሆኑ። ከዚያም ለብልጽግና ካድሬ መልማይ ሆኑ፤ ፍትህ ሚኒስቴር ገቡ፣ ካዘም የሰላም ሚኒስተር ዳኤታ ሆኑ፤ በዚህ ሁሉ ጎዳናዎች ሲያልፉ ልዩ ልዩ ሰው፣ የተለያዩ አንድበቶች ያሉዋቸው ሰው ነበሩ። ሲባረሩ አዲስ ትርክት ይዘው መጡ። ጠያቂዎቻቸው አንዱንም ጉዳይ አንስተው አልሞገቱም። ባይሞግቱም ለአፋቸው ያህል አላነሱም። የትግራይ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ ምስክርነት ሰሞኑን ያሰራጩት ምስክርነት ከስር ያንብቡ።
ጥቅምት 14/2013 ዓ/ም ረፋድ 4፡00 ላይ ሰብሓት ነጋ፡ እኔ እና አንድ ስሙ መጥራት ያልፈለግኩት ብርጋዴል ጀነራል በመቐለ ከተማ አብርሃ ካስትል ሆቴል ውስጥ ቀርስ እየበላን ሰብሓት እና ብርጋዴል ጀነራሉ ስለ ሃገራችን በተለይም ብልፅግና እና ህወሓት ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ጉዳዮች ሲተነትኑ እኔ በምሰማት ላይ ነበርኩ።
በሁለቱም ሰዎች ንግግር መሃል ጀነራሉ ህወሓት ከብልፅግና ጋር ባለው በወቅቱ የመሳሳብ ሁኔታን በማየት ነገሩ የከበዳቸው የሰሜን ዕዝ እንደሆነ ለሰብሃት ነጋ አነሳለት። ሰብሓት ጀነራሉ ላነሳለት የሰሜን ዕዝ ጉዳይ ሲመልስ “ሰሜን ዕዝ ሊያሳስብህ አይገገባም። ምክንያቱም ሰሜን ዕዝ ያሉት ወታደሮች በቁጥር 44 ሺ ነው ፡ እኛ ደግሞ በቁጥር 34 ሺ ልዩ ሃይል አዘጋጅተናል ፡ ከዛም ሰሜን ዕዝ ያለው በህዝባችን መሃል ስለ ሆነ በጠላት ህዝብ ውስጥ ወይም በደጀን ህዝብ ውስጥ አይደለን ያለው። በዚህ ምክንያት ሰሜን ዕዝ technically speaking ሙርከኛ ነው ማለት ይቻላል” በማለት ማብራሪያ ሰጠው ።
እኔ ይህ የሰብሓት ነጋ ማብራሪያ በሰማሁኝ ቅፅበት ዝምታዬን ሰበርኩ ። ሰብሓት የሰጠኸው ማብራሪያ ፍፁም አደገኛ ነው፡ ይህ አባባል በተለይም technically ሙርከኛ ነው ያልከው ሰሜን ዕዝ practically ሙርከኛ ለማድረግ እርምጃ መውሰድን ይጠይቃል። ይህ ማለት ትግራይን ላለፉት 20 ዓመታት ከሻዕቢያ ሲጠብቃት የኖረ ሰራዊት ላይ ክህደት መፈፀም ነው ። ይህ ክህደት ደግሞ ሌሎች ኢትዮጵያዊያንን ፀረ ትግራይ ለማስተባበር የሚጠቅም አጀንዳ መስጠትም ነው። ከዚህ ባለፈ ግና ሰሜን ዕዝ የሚታዘዘው ከአዲስ አበባ ስለ ሆነ በድንገት እርምጃ ተወስዶበት ቢዳከምም አዲስ አበባ ማዕከሉ ያደረገ መላው ኢትዮጵያዊያን የሚያሰባስብ ሰራዊት መልሶ በማደራጀት ጦርነቱ እንዲቀጥል ይደረጋል። ይህ ደግሞ ውሎ አድሮ ህወሓት እንደ ድርጀት ትግራይ እንደ ክልል የሚጎዳ ስሌት ነው የሚል አስተያየት ሰጠሁኝ። ሰብሃት እና ጀነራሉ እስክንለያይ ድረስ ሃሳቤን ከሰጠሁኝ በኋላ ምንም አላሉኝም ። የቀን ውሎ አልቆ ምሽት ሰአት በግምት 3፡00 ሲሆን ሰብሓት ድውሎ ቀን ስላወራነው ነገር ከማንም ጋር ማውራት የለብህም የሚል ማሳሰቢያ ተናገረኝ ።
እንደተባለው ጥቅምት 24/2013ዓ/ም technically ሙርከኛ የሆኖው እና በጠላት ህዝብ መሃል ያለውን ሰሜን ዕዝ practically ሙርከኛ ለማድረግ በህወሓት ወታደራዊ ቋንቋ አነጋገር መሰረት መብረቃዊ ጥቃት ተወሰደበት። ከዛው የሆነው ሆነ ።
ህወሓት መሩ የትግራይ መንግስት በጦርነቱ ተሸንፎ በረሃ ሲገባ በተቋቋመው ጊዚያዊ አሰተዳደር የፍትህ ቢሮ ሃላፊ ሆኜ ከተመደብኩኝ ከሁለት ሳምንት በኋላ የትግራይ ክልል የፀጥታ እና ደህንነት ቢሮ ከአንድ ቢሮውን በደንብ ከሚያቀው ሰው ጋር በመሆን ሄደን አስፈላጊ ናቸው ብዬ ያመንኩባቸው ሰነዶችን ሰበሰብኩኝ። በዋነኛነት የ2011ዓ/ም፡ 2012ዓ/ም እና 2013 ዓ/ም ዓመታዊ ዕቅዶች እና የፋይናንስ ነክ ሰነዶች ናቸው። እነዚህ ሰነዶች ሳገላብጥ ሰብሓት ጥቅምት 14/2013 ዓ/ም የጠቀሰልኝን የልዩ ሃይል ብዛት 34 ሺ ትክክል መሆኑን ከ2013 ዓ/ም ዓመታዊ ዕቅድ አረጋገጥኩኝ። ከተባለው የልዩ ሃይል ቁጥር በተጨማሪ 71ሺ የታጠቀ ሚልሻ እና 91ሺ መሳሪያ የሌለው ተጠባባቂ ምልምል ምልሻ አዘጋጅተው እንደነበር ተረዳሁኝ።
ይህ የሚያሳየው ህወሓት ጦርነቱ መጀመሩ ብቻ ሳይሆን በጦርነት አሽናፊ ሆኖ ለመውጣት አቅሙን የፈቀደው ዝግጅት ከማድረጉም በላይ ሰሜን ዕዝ የመታበት በድንገት ሳይሆን በተሰላ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ዕቅድ መሆኑን ነው መረዳት ችያለሁ።



