ሌብነት ሰዎች ስልጣናቸውን በመጠቀም በነጻ መስጠት ያለባቸውን አገልግሎት ለሃብት ማከማቻነት ሲጠቀሙበት ነው። ይህም አነስተኛ ዝርፊያ መሆኑን ጠቅሰው፥ የመንግስት ሰራተኞች የተሰጣቸውን አደራ ወደ ጎን በመተው ለሚሰጡት አገልግሎት ሲያስከፍሉ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
ሰዎች ያላቸውን የትኛውንም ሙያ እንደመሳሪያ በመጠቀም አላስፈላጊ ጥቅም ለማግኘት ሲሞክሩ ይስተዋላል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ይህም አነስተኛ ሙስና እንደሆነ ተናግረዋል።
የመደመር መንግስት ይህን አይነቱን ሌብነት በአረም መልኩ እንደሚመለከተው ጠቅሰው፥ አረምን ለይቶ ማወቁ ለመንቀል ቀላል ቢያደርገውም ብዛቱ እና ከማሳው ጋር መመሳሰሉ ስራውን አታካች ያደርገዋል ብለዋል፡፡ ይህ አይነቱ ሌብነት ብዙ እና ለልየታ አዳጋች ቢሆንም ከተለየ ለመንቀል ቀላል መሆኑን ገልጸዋል።
ሌላው የሌብነት ዓይነት ከባድ ዝርፊያ መሆኑን በመጥቀስ በግለሰቦችና ቡድኖች መካከል በቅንጅት የሚሰራ ነው ብለዋል፡፡ ይህም አንዳንዶች ስልጣን ይዘው፣ አንዳንዶች ሚዲያ ይዘውና ሌሎች ደግሞ የጦር መሳሪያ ይዘው የሚፈጽሙት የተቀናጀ ዝርፊያ መሆኑን አብራርተዋል። መንግስታት ከባዱን ዝርፊያ ቢመለከቱ እንኳን ለመንቀል ያስቸግራቸዋል ነው ያሉት፡፡
መሰል ዝርፊያዎች እንደ ዋርካ የሚታዩ ሆኖም ግን በቀላሉ ለመንቀል የሚያዳግቱ ሲሆን በሀገር ደረጃ ካደጉ የመንግስትን ፖሊሲና አቅጣጫ የሚወስኑ እንደሆነ ገልጸዋል።
መንግስትም በአቻነት ስሜት የሚያያቸው ይሆናሉ ብለዋል፡፡ ይህም በተለያዩ ሀገራት እንደሚታይ አንስተው፥ በኢትዮጵያም ከለውጡ በፊት በግልጽ ሲታይ እንደነበር አስታውሰዋል።
ባለስልጣናት ከባለሃብቶች ጋር ተመሳጥረው ህግ ሲያወጡና ያሻቸውን ሲዘርፉ የነበሩበት ሁኔታ ነበር ነው ያሉት፡፡ ከለውጡ በኋላ በተሰራው ስራ መሰል ዝርፊያ አለመኖሩን ተናግረዋል።
የመደመር መንግስት በስፋት የሚስተዋለውን አነስተኛ ዝርፊያ ለመንቀል ስርዓት ዘርግቶ ለማስወገድ በስፋት እየሰራ ነው ብለዋል፡፡ በመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትን ጨምሮ ሞባይል ባንኪንግና ዘመናዊ ግብይቶች መፈጠራቸው ችግሩን ይቀርፋል ነው ያሉት፡፡
“ኢትዮጵያ የፌደራል ስርዓት ከጀመረች ከ30 ዓመት ቢያልፋትም ስርዓቱ ዛሬም ጥያቄ አለበት”
የመጀመሪያው የፊውዳል ስርዓት፣ የሪፐብሊክ ስርዓት እና የፌደራል ስርዓት ናቸው፤ አንድን ስርዓት የማፍረሱ ጉዳይ በተወሰኑ ዓመታት ተከውኖ የማያልቅ መሆኑን ለመገንዘብ ኢትዮጵያ የፌደራል ስርዓት ከጀመረች ከ30 ዓመት ቢያልፋትም ዛሬም የፌደራል ስርዓቱ ጥያቄ አለበት።
ኢትዮጵያ የነበረችበት አካሄድ አንዱ የሌላኛውን ማፍረስ ላይ ያተኮረ ነው፤ ይህም የተቋማት ቅቡልነትን በማሳጣት የባህል መበስበሰሰ እና የኢኮኖሚ ውድቀት አድርሷል
“የመደመር ሐሳብ በተለያየ ደረጃ ሊተገበር የሚችል ሐሳብ ነው።”
ሰው በግሉ፣ በቤተሰቡ አልያም በቡድን የመደመርን ፅንሰ ሐሳብ ተለማምዶ ሊተገብረው ይችላል። የመደመርን ፅንሰ ሐሳብ በግሌ የተለማመዱት እናም በሰራሁበት ተቋማት የተጠቀምኩበት እንዲሁም ፍሬ ያፈራሁበት ሐሳብ ነው። ፅንሰ ሐሳቡ ወደ መንግሥት ሐሳብነት ያደገው በሂደት ነው፤ ከግል እና ከውስን የመሥሪያ ቦታዎች አልፎ የመንግሥት አቋም ለመሆን በርከት ያለ ጊዜ ወስዷል።
የመደመር ፅንሰ ሐሳብ መጽሐፍ ሆኖ ሳይወጣ በብዙ ሥልጠናዎች፣ ውይይቶች፣ ሰነዶችን በማገላበጥ፣ በተጨማሪ ንባቦች እና ምልከታዎች በማድረግ በሂደት ቀመሩ እየዳበረ፣ እያደገ እና እየሰፋ መጥቶ መጽሐፍ ሊሆን ችሏል፡፡ ሐሳቡን የጥቂት ሰዎች ብቻ ሳይሆን ብዙዎች የሚቀበሉት እና የሚያምኑበት፤ የሚሥሩበት እና የሚጠብቁት የወል ሐሳብ ለማድረግ በርካታ ሥራዎች ተሠርተዋል።
“ፖለቲካ በጥላቻና ስሜት ሳይሆን በሃሳብ የበላይነት መመራት አለበት”
ፖለቲካ እንደሸቀጥ የሚሸቀጥበት ሥርዓት ከሃሳብ የራቀ መሆኑን በማስረዳት፣ ሊከሰት የሚችልን አደጋና ብሔራዊ ጥቅም ማስከበር ላይ የራሱ እይታ አለው፡፡ እንደ ሀገር ሀገራዊ ትርክት መፍጠር እስካልተቻለ ድረስ ኢትዮጵያን በምንፈልገው ልክ አስቀምጠን ጥቅማችንን ለማስከበር ያለውን ፈተና እና መውጫ መንገዶችን ያሳያል፡፡
ፖለቲካ በግል ጥላቻና ስሜት ሳይሆን በሃሳብ የበላይነት መመራት እንዳለበት አጽንኦት የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ ሀገራዊ፣ የወል እና አሰባሳቢ ትርክት መገንባት ይገባል።

