Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  OPINION  ‹‹ወልቃይትን በዐማራ መቃብር ላይ ካልሆነ አታስቡት… ራሳችንን ለመከላከል ተዘጋጅተናል›› አሸተ ደምለው
OPINION

‹‹ወልቃይትን በዐማራ መቃብር ላይ ካልሆነ አታስቡት… ራሳችንን ለመከላከል ተዘጋጅተናል›› አሸተ ደምለው

Ethioreview newsEthioreview news—January 30, 2026
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የወልቃይት ጠገዴ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሸተ ደምለው ከትግራይ አቅጣጫ እየተነሳ ነው የሉትን የጦርነት አካሄድ አስመልክቶ ሁለት ስለት ያለው ሰይፍ ሲሉ የዘረዘሩትን አቋም ይፋ አድረገዋል። ጽሁፉ የተላከው ለአንዳፍታ ሚዲያ ሲሆን እንዳለ ወስደን አቅርበነዋል።

የወልቃይ ጠገዴ የዘመናት የአማራ ማንነትና ወሰን ጥያቄ የተለያዩ የትግል ምዕራፎችን አልፎ ዛሬ ወሳኝ የትግል ሜዳ ላይ ደርሷል፡፡

ዛሬ የደረስንበት የትግል ሜዳ የወትሮ ዝግጁነትን በማሳደግ በሁለት የትጥቅ አቅሞች ልቆ መገኘትን ይጠይቃል፡፡

አንደኛው በሀሳብ ትጥቅ ሲሆን፤ ሁለተኛ ደግሞ ከአባቶቻችን በወረስነው አርበኝነት መሰረት ራስን መከላከል ላይ መሰረት ያደረገ አቅምና ተነቃነቃዊ ዝግጁነትን ማሳደግ የሚጠይቅ ወሳኝ የትግል ጊዜ ላይ ነን፡፡ የሀሳብ ትጥቁም ሆነ ራስን ከወረራ የመከላከል ዝግጁነቱ መዳረሻ ግቡ የተከዜ አዳኝ ትውልድ ተልዕኮን ማሳካት ነው፡፡  ተልዕኳችን ደግሞ ‹ለመጭው ትውልድ ነጻነትን እንጂ ተሻጋሪ ዕዳን አናወርስም› የሚል ዘላቂ አሸናፊነትን ያለመ ነው፡፡  ዘላቂ አሸናፊነት ስንል በሁለት መልኩ ነው፡፡

More stories

“በነዉጥና በኃይል የበለፀገ ሀገር የለም”

May 2, 2023

ወያኔያዊ አማራነትን አማራ “አማራ ነኝ”

December 6, 2022

ሰውን “ሰው” የሚያደርገው ምንድነው? ከእኛ ይልቅ የጥንቶቹ ዘመናዊ ነበሩ

November 1, 2024

ወግ አጥባቂው የኦክላሆማ ሴናትር ማ’ናቸው?

October 6, 2022

በአንደኛው ገጽ ዘላቂ የሕግ አሸናፊነት ሲሆን፤ ሁለተኛው ገጽ ደግሞ የሕግ አሸናፊነታችንን አልቀበልም ብሎ ለዳግም ወረራ የሚነሳውን ኃይል የምንመክትበት ራስን የመሆን ክቡር ሰማዕትነትን ልንቀበልበት የተዘጋጀንለት የፀረ-ወረራ ተጋድሏችን ነው፡፡

እናም የተከዜ አዳኝ ትውልድ ሚና በሁለት ገጽ የተሳለ ሰይፍ ማለት ነው፡፡ በሀሳብ ትጥቅም ሆነ በራስ መከላከል ትጥቅ፤ ሁሌም ዝግጁ ሆኖ መገኘት!!

የሀሳብ ትጥቅ ስንል ምን ማለታችን ነው…?

የወልቃይት-ጠገዴን አማራነት ከታሪክ፤ ከመሬት ይዞታ፤ ከአስተዳደርና ከግብር ክፍያ፤ ከመልክዓ-ምድራዊ፤ ከሕዝብ ስርጭት፤ ከሥነ-ልቦናና ቱባ ባህላችን፣… ወዘተ ማመሳከሪያዎች አንጻር ወልቃይት-ጠገዴ አማራ እንጅ ትግሬ ሆኖ እንደማያውቅ በወያኔ የሐሰት ትርክት ለተደናገሩ ለሌሎች የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች በማስረዳት፤ ለዓለማቀፉ ማኀበረሰብ ማስገንዘብን ዋና ማዕከሉ ያደረገ የትግል ክፍል ነው፡፡ በዚህ የትግል ክፍል ውስጥ ታሪክ ትልቅ ቦታ ይሰጠዋል፡፡

ይህ የሚሆነው፡- ታሪኩን ጠንቅቆ የሚያውቅ ትውልድ ጉድለቱን ይሞላል፡፡ የትግል ስንቅ ባለቤት ይሆናል በሚል እሳቤ ነው፡፡ ራስን የመገንዘብ፣ አቅምን የማወቅ፣ ጸጋና በረከትን ለይቶ የመጠቀም፣ የሀሳብም የተግባርም ጉልበት ይኖረዋል፡፡

የሀሳብ ጉልበት ማለት የሀሳብ ትጥቅ ማለት ነው!! የሀገር ባለቤትነት ማረጋገጫ አንዱና ዋናው ጉዳይ ማንነትና ርስትን የማስከበር ጉዳይ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ታሪክን፣ መነሻን ከማወቅ ይጀምራል፡፡ ታሪክና መነሻን ማወቅ ማንነትንና ርስትን ለማስከበር ትልቅ አቅም ነው፡፡

የዚህ ትልቅ አቅም ባለቤት መሆን ደግሞ የሀገር ባለቤትነትን ያረጋግጣል!!

የሀገር ባለቤት ለመሆን የሀሳብ ትጥቅ ያስፈልጋል፡፡

ራስን የመከላከል አቅም መገንባት ስንል ምን ማለት ነው…?

ትግላችን ራስን የመሆን ክቡር የማንነት ትግል ነው፤ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን ትግል ነው፡፡ ነገር ግን ይህን ለዘላቂ የሕግ አሸናፊነት የሚያበቃንን ሰላማዊ የትግል መንገድ አልቀበልም ብለው፤ ዳግም ለወረራ ተከዜን የሚሻገር ወራሪን የምናሳፍርበት፤ የፀረ-ወረራ ትግላችን መመከቻ ነው፡፡

ምክንያቱም ለወረራ እየተዘጋጀ ያለው ኃይል  ትግሉ የእርሱ ያልሆነን ርስትና ማንነት የመውረር የማጥፋት ነው፡፡

በመሆኑም ይህ መምጫው ብዙ የሆነ ኃይል ሊመከት የሚችለው  የትግል ዓላማ ጥራት ባለው በተደራጀ፤ የአመራር ተዋረድ ባለው፤  የታሪክና የትውልድን ጥያቄ በዘላቂነት ሊመልስ በሚችል ጠንካራ አደረጃጀት እንጂ እንዲሁ በተበተነና ባልተቀናጀ መልኩ በሚደረግ ትግል ማሸነፍ አይቻልም፡፡ 

ሕግና ሥርዓት ባለው መንግሥታዊ መዋቅር፣ ተዋረዳዊ ባለው አመራር ራስን የመሆን ክቡር ማንነታችን በዘላቂነት ይረጋገጣል ስንልም እውነት ሁሌም አሸናፊ እንደምታደርግ በመተማመን ነው።

የወልቃይት-ጠገዴ የአማራ ማንነትና ወሰን በዘላቂነት የማስከበር ትግል ከመቼውም ጊዜ በላይ ሕዝባዊ አንድነትና ስትራቴጂያዊ አመራር ይጠይቃል፡፡

እስካሁን በመጣንበት መንገድ፡- የወልቃይት-ጠገዴ የአማራ ማንነትና ወሰን ትግል ከከፋኝ የአርበኞች ተጋድሎ እስከ የማንነት አስመላሽ ኮሚቴው ሰላማዊ የትግል መንገድ፤ የሰሜን ዕዝ ከጀርባ መታረድን ተከትሎ በሕግ-ማስከበር ዘመቻው አገርን ከጥቃት፣ ራስን ደግሞ ከወራሪው ህወሓት የባርነት አገዛዝ ነፃ ለማውጣት ከተከፈለው መስዋዕትነት እስከ አሁን ድረስ ለዘለቀው የወልቃይት-ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ምስረታና በራስ ልጆች የመተዳደር ዕድል በጋራ መስዋዕትነታችን፣ በትግል ዓላማ ጽናታችን እዚህ ደረጃ ላይ ደርሰናል፡፡

ዛሬ የወልቃይት-ጠገዴ የአማራ ማንነት ጥያቄ ከኢትዮጵያ አልፎ በአፍሪካ ቀንድ ወሳኝ ከሚባሉ ጉዳዮች አንዱ ሆኗል፡፡

በትግላችን የአማራን ሕዝብና ፍትሕ ወዳድ የሆኑ ኢትዮጵያዊያንን ከጎናችን ማሰለፍ ችለናል፡፡ የማንነት ኮሚቴው ሰላማዊ የትግል መስመሩን ጠብቆ በመጓዝ ላይ ነው፡፡ የዞኑ አስተዳደር ህጋዊነትን ተላብሶ በሕግና በሥርዓት ሕዝብ እያስተዳደረ ይገኛል።

በወልቃይት ጠገዴ ጉዳይ በርካታ ዓለማቀፍ ኃይሎች ጫና ቢያሳድሩም ሕዝብን ይዞ የተሸነፈ የለምና ዛሬ በትግላችን ቀና ብለን መሄድ ጀምረናል፡፡

እንደሰው ተከብሮ ከመኖር፣ በባህል፣ ወግና ቋንቋችን ከመጠቀም አልፈን የሕዝባችንን የዘመናት የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች እንዲሟሉ በራስ ተነሳሽነት በአቅማችን እየታገልን እንገኛለን፡፡  የክልላችን መንግሥት አቅሙ የፈቀደውን ድጋፍ በማድረግ ላይ ነው። የፌዴራል መንግሥቱ አንደኛውን አንገብጋቢ ጥያቄ በኢትዮጵያ አየር መንገድ በኩል ምላሽ ሰጥቶናል። ለዚህም በመላው የወልቃይት ጠገዴ አማራ ሕዝብና አስተዳደር ሥም እናመሰግናለን።

ሌሎች የመሰረተ ልማት ድጋፎች እንደሚቀጥሉ እምነት አለን። በእኛ በኩል የትግል ቁርጠኝነታችን ጸንተን፣ የአገር ውስጥና የውጭ ዲያስፖራ ወገናችንን በማስተባበር በውስጥ አቅም ራስን ሆኖ መገኘት በሚለው መርሆችን የሕዝብ አቅምን ለሕዝብ ጥቅም አሟጠን ለመጠቀም እንተጋለን።

በጥቅሉ ዛሬ የወልቃይት-ጠገዴ ሲቲት ሁመራ ዞን አስተዳደርና ሕዝብ ‹በአንድ እጅ ነጻነት፣ በሌላው እጅ ልማትን ማረጋገጥ› እንደሚቻል በተግባር ማሳየት ችለናል፡፡

ቀን የእርሻ ቦታ ሌሊት ምሽግ እያደሩ ራስን ከመጠበቅ አልፎ ለኢትዮጵያ አገረ-መንግሥት ብሔራዊ ዘብ፤ ዳር ድንበር ጠባቂ መሆኑን የአባቶቹን ታሪክ በተግባር በመድገም ማስመስከሩን ቀጥሏል፡፡

ይሁን እንጂ በዚህ ሁሉ ድል መሀል ጠላት ዛሬም ዓይኑን ከእኛ ላይ አልነቀለም፡፡

ከሦስት አስርት ዓመታት በላይ ከአፓርታይድ በከፋ ሁኔታ ረግጦ ይገዛው የነበረውን ወልቃይት ጠገዴን ዳግም ተመልሶ ለመቆጣጠር የተለያዩ የፖለቲካ ሴራዎችን አለፍ ሲልም የኃይል አማራጭን ታሳቢ ያደረገ እንቅስቃሴን ያልማል። 

ዛሬም ለዳግም ወረራ ታጣቂ ኃይሉን ተከዜን ለማሻገር የተጠና የፖለቲካ ስልት፤ የማደናገሪያ ፕሮፖጋንዳዎችን በመልቀቅ ላይ ነው፡፡

ይህ ኃይል ፍላጎቱ፣ ወልቃይት ጠገዴን መልሶ በመቆጣጠር ዛሬም እንደ ትናንቱ ከሰው በታች ሊያደርገን፤ ሊያዋርደን፤ ብቻ አይደለም፡፡ እንደሕዝብ ጨርሶ ሊያጠፋን ነው ፍላጎቱ፡፡

ይህ ደግሞ በወልቃት-ጠገዴ አማራ ሕዝብ መቃብር ላይ እንጅ የማይታሰብ ጉዳይ ነው!!

በመሆኑም ሁሌም ዝግጁ ሆኖ መገኘት በሚለው የትግላችን መርህ መሠረት፡- ለፍቅርም ሆነ ራስን ለመከላከል አንቦዝንም።

በህብረ ብሄራዊ አንድነት አብሮነትን የሚሹ እህት ወንድሞቻችንን እንቀበላለን፥ የኃይል አማራጭን አስበው ለወረራ የሚዘምቱ ካሉም አንታገስም።

በዞናችን የሚገኘውን ሁሉንም የትግል አቅም ወደአንድ የአመራር ቋት በማምጣት ለዘላቂ ድል የሚያበቃ የትግል ስትራቴጂ ለመከተል በምናደርገው ህጋዊና ሰላማዊ ትግል ውስጥ ሁሌም ከጎናችን የቆማችሁ መላው የአማራ ህዝብ፣ መላው የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችን እናመሰግናለን።

እንደ ዶክተር ዳኛቸው አሰፋ፣ እንደ ጋዜጠኛና ደራሲ ገነት አየለ ያሉ የሀሳብ ፊት አውራሪዎች የተከዜ አዳኝ ትውልድ በዕድሜ፣ በፆታ፣ በኃይማኖት፣ በጊዜ፣ በቦታ እንደማይወሰን፤ ብረት ብቻ ሳይሆን እውነትን ይዞ በሀሳብ መታገል እንደሚቻል ማሳያዎቻችን ናቸው።

እኒህን የመሰሉ ምሁራዊ ህዝባዊነትን የተላበሱ ወገኖቻችን፦ የትግል አበርክቷቸው በወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነት ትግል ውስጥ መቼም፣ የትም በምንም ሁኔታ ከእውነት ጋር የመቆም የፍትሐዊ ትግል አካል የመሆን የሞራል ጉዳይ ስለመሆኑ ማሳያዎች ናቸው።

የትግሉ ዋና መርህ የወልቃይት ጠገዴ አማራ ማንነት የትግል መርህ፡- ሁሌም ዝግጁ ሆኖ መገኘት!

በምሽግ ውለው የሚያድሩ ታጋዮች በሚናቸው፤

በሀሳብ ፊት አውራሪነት ለእውነት የቆሙ ታጋዮችም በሚናቸው የተከዜ ዘብ ሆነው ይዘልቃሉ!!

ጠፍጣፋ ድንጋይ መሮ አይበሳው፣

የአባቱን ታሪክ ልጁ አይረሳውም” ብለን እንደ ብረት የጠነከረ አንድነትን ይዘን በጠላት አጀንዳና ፕሮፖጋንዳ አንደናገርም፣ ከትግላችን ዓላማም ንቅንቅ አንልም።

(ማስታወሻ፡- ይህ ሀሳብ የዋና አስተዳዳሪውን አቋም እንጂ የዝግጅት ክፍል አቋም እንዳልሆነ አስቀድመን ለማሳወቅ እንወዳለን፣ ተቃራኒ ወይም ተመሳሳይ አሳብ ካለ እናስተናግዳለን )

OPINION
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
“በወጣቶች ሕይወት መነገድ ይበቃል!” – ስምረት ፓርቲ
የአርሚ 11 አዛዥ ሌ/ጄኔራል ፍስሃ በየነ እጅ ለመስጠት ከመከላከያ ጋር ንግግር መጀመራቸው ተሰማ፤
Related posts
  • Related posts
  • More from author
OPINION

እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ…

April 8, 2026
OPINION

ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት!

April 8, 2026
OPINION

ሙስጠፌ ተረኛው ባለስልጣን – የሃሰት ትርክ ዘመቻ በደቦ

March 28, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2