Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  ማህደር  ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም
ማህደር

ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም

Ethioreview newsEthioreview news—September 10, 2023
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የኢትዮጵያ ክብርና ነፃነት በቆራጥ ልጆቿ መሥዋዕትነት የተገኘ መሆኑ የማያጠያይቅ ነው፡፡ ለሀገራችን ሠላም፣ ለሠንደቅ ዓላማችን ክብር ሲሉ መሥዋዕትነት ከከፈሉ ጀግና ኢትዮጵያውያን መካከል ደግሞ ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ሃብተማርያም አንዱ ናቸው፡፡ ዛሬ ጳጉሜ 2 ለኢትዮጵያ ሀገራቸው መሥዋዕትነት የከፈሉ ጀግኖች የሚታሰቡበት እና የሚዘከሩበት ቀን እንደመሆኑ በዛሬው የአውደ ሰብ አምዳችን ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ሃብተማርያምን ባለታሪካችን አድርገናቸዋል፡፡

ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ሀብተማርያም ተወልደው ያደጉት በጉራጌ ዞን ከቸሀ ወረዳ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ሲሰ መንደር ውስጥ ነው፡፡ እስከ 8ኛ ክፍል ያለውን ትምህርታቸውን እዚያው እምድብር ከተማ የተማሩ ሲሆን፣ በ1948 ዓመተ ምህረት የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ተፈትነው በጥሩ ውጤት አጠናቀዋል፡፡

የ8ኛ ክፍል ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁም የአምቦ እርሻ ልማት ትምህርት ገብተው ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፤ በኋላም ወደ ጦር አካዳሚ በመግባት የ3 ዓመት ወታደራዊ ሳይንስና የአካዳሚ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁት በስመጥሩው የምርጥ መኮንኖች ማፍሪያ በሆነው ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ (ሀረር) ጦር አካዳሚ ነው። 

ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ በመቀጠልም የጦር ሠራዊቱን በመቀላቀል የአየር ወለድ ሥልጠና የወሰዱ ሲሆን፤ ሙያቸውን ለማጠናከርም በእስራኤል የኮማንዶ ትምህርት፣ አሜሪካ የልዩ ኃይል፣ ሞስኮ እና ህንድን ጨምሮ በተለያዩ የውትድርና ሥልጠናዎችን ራሳቸውን አብቅተዋል፡፡  

More stories

የረቂቅ ሙዚቃ ስፔሻሊስት (ጥቁሩ ኮዳይ)

June 9, 2024

ባለ ገድሏ ሸዋረገድ ገድሌ

November 4, 2024

የሦስት ሊቃውንት የአሻራ ቅብብሎሽ

October 5, 2025

ከተማ ይፍሩ – ያልተነገረላቸዉ የአፍሪቃ አንድነት መስራችና ዲፕሎማት

June 6, 2023

በ1969 ዓ.ም የሶማሊያ ተስፋፊ ሃይል ኢትዮጵያን ወሮ ከጅግጅጋ እና ጎዴ አልፎ መጥቶ እስከ ሜኢሶ ድረስ በመቅረብ መሬቱን በፈንጅ አጥሮ ነበር፡፡ ይህ መሰናከል ለሠራዊቱ እና ለህዝቡ መሰረታዊ የሆኑ ነገሮች ለማቅረብ በጣም ችግር ፈጠረ፡፡ ይህን ችግር ለመፍታትም የሶማሊያ ግዛት ክልል ውስጥ ዘልቆ መግባት እና ፈንጅ መቅበር አንድ መንገድ የነበረ ሲሆን፣ ይህ ግዳጅም ለብ/ጀነራል ተስፋዬ ተሰጠ፡፡ እሳቸው የሚመሩት ቡድንም ድንበር አቋርጦ ሶስት ቀን እና ሌሊት ፈንጂ በመቅበር የጠላትን እንቅስቃሴ አወከ፤ ትልቅ ውጤትም ማምጣት ተቻለ፡፡

በ1970ዎቹ መግቢያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በጠለፋ ምክንያት በጣም በከፍተኛ ሁኔታ ችግር ውስጥ ገብቶ የነበረ ሲሆን፣ በዚህም አንዳንድ ቦታዎች ላይ በረራ በመቆሙ ድርጅቱ ለሠራተኞቹ እንኳን ደሞዝ መክፈል ያልተቻለበት ሁኔታ ላይ ደርሶ ነበር፡፡ ችግሩን ለመፍታትም የበረራ ደህንነት እንዲቋቋም መንግሥት ሲወስን የድህንነት ቡድን እንዲያቋቁም ለብ/ጀነራል ተስፋዬ ኃላፊነት ተሰጣቸው፤ እሳቸውም የሰለጠኑ የደህንነት አባላት ከአውሮፕላኖቹ ጋር እንዲጓዙ በማድረግ ችግሮቹን መፍታት ችለዋል፡፡

በሰላም ለመኖር መሰረቱ ሥነ- ሥርዓት ነው የሚሉት ብርጋዴን ጄኔራል ተስፋዬ ሀ/ማርያም “በኢትዮጵያ ምድር ውስጥ ጥይት በሚፈነዳበት ቦታ ሁሉ እኔ ያልተሳተፍኩበት በጣም ጥቂት ሲሆን፣ አብዛኛው በተሳተፍኩባቸው ቦታዎች በድል ወይም በስኬት ነው የተጠናቀቁት” በማለት ስለ ህይወት ተሞክሮአቸው ይገልጻሉ፡፡

በ1970ዎቹ እርሳቸው የሚመሩት የአየር ወለድ ጦር ናቅፋ ተራራ ላይ ለ6 ወራት በጠላት ተከቦ በህይወት ቆይቶ የጠላትን ከበባ ሰብሮ በህይወት እንደወጣ ሲነገሩ፣ ይህ ታሪካዊ ክስተት በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የተፈጠረ የአየር ወለድ ሠራዊት ጀብድ እንደሆነ ይገልጻሉ፡፡   

ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ሃ/ማርያም በሶማሊያ ጦርነት ወቅት ለሠሩት ገድል እና በናቅፋ በሰሩት ጀብድና የአመራር ብቃት ከሻለቃነት ወደ ኮሎኔልነት በአንዴ ማደግ የቻሉ ወይም በ5 ዓመት የሚደረስበትን ወታደራዊ ማዕረግ በፈጥነት ማግኘት የቻሉ ጀግና ናቸው፡፡ ጀነራሉ በኢትዮጵያ ታሪክ ለማንም ወታደር እና መኮንን ተሸልሞ የማያውቀውን “ወደር የሌለውን የሕብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና ወታደራዊ ሜዳሊያም” ተሸልመዋል፡፡

ማንም ሰው ብቁ አሰልጣኝ ካገኝ አየር ወለድ መሆን እንደሚችል የሚገልጹት ብ/ጀነራል ተስፋዬ፣ እሳቸው ከሀረር ጦር አካዳሚ በመሰረታዊ ውትድርና ከሰለጠኑ በኋላ የአየር ወለድ ሥልጠና ያገኙት ከእስራኤሎች እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ 

“ኢትዮጵያ በየዘመኑ ጀግና የምታፈራ የጀግኖች ሀገር ናት” የሚሉት ብ/ጀነራል ተስፋዬ ሀብተማርያም ለዚህም መላው የሀገሪቱ ህዝብ ትልቅ ኩራት ሊሰማውና ተስፋ ሊሰንቅ እንደሚገባም ይናገራሉ።

“የሀገሪቱን ዕድገት ጎታች ሆኖ ፈተና ውስጥ የከተተን ነገር የእናት ጡት ነካሽ በሆኑ ከሀዲዎች በየጊዜው የሚከፈትብን ጦርነት ነው፤ ይህንን የህልውናችንን ጠላት ለመዋጋት ደግሞ ወጣቱ ከጦር ሜዳው ተሳትፎ ባልተናነሰ መልኩ መነሳትና አንድነት መፍጠር ይኖርበታል” ይላሉ። (ኢዜአ)


  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
    ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም።… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
    አዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
    ለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
    ቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች
    ቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን ዶላር ሃብት “የሂሳብ… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
Why G20’s debt-relief strategy is failing
“የሕዳሴው ግድብ አብይ ሸጦታል” አቶ ጌታቸው
Related posts
  • Related posts
  • More from author
Events

የመደመር መንግሥት አዕማዶች – የመጽሐፍ ዳሰሳ

October 8, 2025
ማህደር

የሦስት ሊቃውንት የአሻራ ቅብብሎሽ

October 5, 2025
ማህደር

“ኦሮሞ ‘ፈጣሪ ጥቁር ነው’ ይላል” የዋቄፈና እምነት

October 4, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • INTERVIEW
    • law
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • ያበደው
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2